Your cart is currently empty!
ተስፋ ብርሃን ህፃናትና ቤተሰብ ልማት ድርጅት ከቻይልድ ፈንድ ጋር በመተባበር በትግራይ ክልል፣ ምስራቃዊ ዞን አዲግራት ከተማ ለሚተገብረው ፕሮጀክት የሴቶች ንፅህና መጠበቂያ ኪት (Dignity Kit) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Reporter(Aug 17, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ተስፋ ብርሃን ህፃናትና ቤተሰብ ልማት ድርጅት 2ኛ ዙር የግዢ ጨረታ ማስታወቂያ
ተስፋ ብርሃን ህፃናትና ቤተሰብ ልማት ድርጅት ከቻይልድ ፈንድ ጋር በመተባበር በትግራይ ክልል፣ ምስራቃዊ ዞን አዲግራት ከተማ ለሚተገብረው ፕሮጀክት የሴቶች ንፅህና መጠበቂያ ኪት (Dignity Kit) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም በመስኩ የተሠማራችሁና በጨረታሙ ለመሳተፍ የምትፈልጉ
1) በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ
2) የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምዝገባ ሰርትፊኬት እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN)
3) የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማሰረጃ በማቅረብ
ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 (ሰባት) ተከታታይ ቀናት ውስጥ፣ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) ብቻ ቀይት በሚገኘው ከድርጅቱ ዋና ጽ/ቤት፣ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ ቀኑ 11፡30 ሰዓት ባስሙ የሥራ ሰዓት በመቅረብ መግዛት ይችላሉ። በተጨማሪም፣ የጨረታ ሰነዱን በኢሜይል አድራሻ procurement@tesfab.org በመጠየቅ እና የጨረታ ሰነዱን ዋጋ በባንክ ገቢ በማድረግ ማግኘት ይቻላል። ተጫራቾች የጨረታ ዝርዝሩን ከሰነዱ በማየትና በመሙላት፣ በደብረ ብርሃን ስዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እንዲሁም በመቀሌና አዲስ አበባ በሚገኝ የቻይልድ ፈንድ ቢሮ ዋናውን እና ኮፒውን ማስገባት የሚችሉ መሆኑን በአክብሮት ይገልፃል።
ተጫራቾች የጠቅላላ የጨረታ ዋጋቸውን 2% (ሁለት በመቶ) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) በ”ተስፋ ብርሃን ህፃናትና ቤተሰብ ስማት ድርጅት” ስም አሰርተው ማስያዝ አለባቸው። ጨረታው በ8ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ላይ የመጨረሻው የሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ተዘግቶ፣ ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት ሳይ ጨረታውን ለመካፈል በተገኙ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ፊት ይከፈታል።
ማሳሰቢያ፡ ድርጅቱ የተሻስ አማራጭ ካገኘ በጨረታው ውጤት አይገደድም።
አድራሻ፡ ተስፋ ብርሃን ህፃናትና ቤተሰብ ልማት ድርጅት
ደብረ ብርሃን፣ ቀይት ዋና ጽ/ቤት
ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም።
ተስፋ ብርሃን ህፃናትና ቤተሰብ ልማት ድርጅት