Your cart is currently empty!
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ጽ/ቤት ለወልድያ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ አገልግሎት የሚውል ቤት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል
Addis Zemen(Aug 18, 2025)
Please read the detailed instructions below.ከስር የተቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የቤት ኪራይ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ጽ/ቤት ለወልድያ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ አገልግሎት የሚውል ቤት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል።
ስለሆነም የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና ህጋዊ የባለቤትነት ካርታ ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች ወልድያ ከተማ በሚገኘው በመንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ወልድያ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በመምጣት የማይመለስ ብር 50/ ሃምሳ ብር / በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
ተጫራቾች የተዘጋጀውን የቴክኒከ ማወዳደሪያ ቅጽ በመሙላት፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ህጋዊ ማስረጃ እና ህጋዊ የባለቤትነት ካርታ በኦሪጅናል ፖስታ እንዲሁም የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ የሞሉባትን በሌላ ኦሪጅናል ፖስታ በማሸግና ለሁለቱም ፖስታዎች ኮፒ ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን 11፡00 ድረስ ወልድያ ከተማ አዳጎ ቤተክህነት ህንፃ ወልድያ የመንግስት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር በቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
ጨረታው በ15ኛ ቀን 11፡00 ላይ ተዘግቶ በ16ኛው ቀን 2፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ሲሆን 16ኛው ቀን የባዕል ወይም የዕረፍት ቀን ከሆነ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።
ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 10,000 /አስር ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ የከፈለበትን ደረሰኝ ከቴክኒክ መወዳደሪያ ኦሪጅናል ሀሳባቸው ጋር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
ማሳሰቢያ፡– አስተዳደሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፡–
- ወልድያ ስ/ቁ 033 331 0006
- ደሴ ሰ/ቁ 033 312 0912
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት ሰራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ጽ/ቤት