የቴፒ አጠቃላይ ሆስፒታል በ2018 ዓ.ም ለሆስፒታል አገልግሎት የሚውል የፅዳት እቃዎች፣ የፅህፈት መሳሪያዎች፣ ጄኔሬተር (12KV)፣ የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen(Aug 22, 2025)

Please read the detailed instructions below. ከስር የተቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።

የጨረታ ማስታወቂያ

የቴፒ አጠቃላይ ሆስፒታል በ2018 ዓ.ም ለሆስፒታል አገልግሎት የሚውል የፅዳት እቃዎች፣ የፅህፈት መሳሪያዎች፣ ጄኔሬተር (12KV)፣ የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

በዚሁ መሰረት የጨረታ መስፈርቱን የሚያሟሉ ተጫራቾችን እንዲወዳደሩ ይጋብዛል:

  1. በመስኩ ህጋዊ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸውና የ2018 በጀት ዓመት የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፤ በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸው | የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው።
  2. TIN NUMBER ያላቸው፣
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዳቸው ብር 5,000 /አምስት ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ CPO ማስያዝ አለባቸው፡፡
  4. ንብረቶችን እስከ ቦታው ድረስ ማቅረብ የሚችሉ፤
  5. የጨረታ ውል ማስከበሪያ 10% ማስያዝ የሚችሉ፤
  6. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የስራ ቀናት ሁሉንም ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል ከቴፒ አጠቃላይ ሆስፒታል ግ/ፋ/ን/አስተዳደር ቢሮ ቁጥር 40 መግዛት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ኦሪጅናል በታሸገ በፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። 
  8. የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው የስራ ቀን በ10፡00 ሰዓት ጨረታው ተዘግቶ በሚቀጥለው የስራ ቀን በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቴፒ አጠቃላይ ሆስፒታል ግ/ፋ/ን/አስተዳደር ቢሮ በይፋይከፈታል። ዕለቱ በዓል/ ዝግ ከሆነ በቀጣይ የስራ ቀን ጨረታው ይከፈታል።
  9. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ/ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት በሸካ ዞን የቴፒ አጠቃላይ ሆስፒታል