Your cart is currently empty!
በአብክመ ሰሜን ሸዋ ዞን የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በስሩ ላሉ ሴክተር ጽ/ቤቶች የጽሕፈት መሣሪያዎች፣ አላቂ የቢሮ ዕቃዎች እና የጽዳት እቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Aug 31, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 01/2018
በአብክመ ሰሜን ሸዋ ዞን የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በስሩ ላሉ ሴክተር ጽ/ቤቶች
- የጽሕፈት መሣሪያዎች፣
- አላቂ የቢሮ ዕቃዎች እና
- የጽዳት እቃ፣ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም
- በዘርፉ የወጣ ንግድ ፈቃድና በዘመኑ የታደሰ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የምትችሉ
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን) ፣ ግዥው ከ200,000 /ከሁለት መቶ ሺህ ብር በላይ መሆኑ ሲታመን ተጫራቹ የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ በማድረግ ማቅረብ የሚችሉ፤
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-2 የተዘረዘሩትን ማስረጃዎችን በግልጽ የሚታይ ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ ዕቃዎች አይነትና ዝርዝር መግሎጫ ስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች በቀረበው ዝርዝር መሰረት ለጽ/መሣሪያና አላቂ የቢሮ እቃ ብር 25,000 /ሃያ አምስት ሺህ ብር/ እና ለጽዳት እቃ ብር 1000/አንድ ሺህ ብር ብቻ/ የጨረታ ማስከበሪያ በCPO ወይም በጥሬ ገንዘብ በአጣ/ከ /አስ/ገንዘብ ጽ/ቤት ገቢ በማድረግ /CPO በማሠራት የደረሰኙን ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የምትችሉ፡፡
- የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 300 (ሶስት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ከአጣ ከ አስ ገንዘብ ጽ/ቤት መውሰድ ትችላላችሁ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በታሸገ ፖስታ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ሰዓት ከአጣ ከ አስ ገንዘብ ጽቤት ዘወትር በሥራ ሰዓት በመቅረብ መግዛትና ለዚሁ በተዘጋጀው በጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ትችላላችሁ፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ታሽጎ በዚሁ ዕለት በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታው ይከፈታል፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በራሳቸው የዋጋ ማቅረቢያ ሞልተው ማቅረብ አይችሉም፡፡
- መ/ቤቱ ግዥውን በ26 ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል፡፡
- በጨረታ አሸናፈው ተጫራች ለጽ/ቤቱ ባቀረበው የዋጋ ዝርዝር ከጠቅላላ ዋጋ ከነቫቱ 10% የውል ማስከበሪያ በ CPO ወይም በጥሬ ገንዘብ ብቻ በማስያዝ ውል የመፈረም ግዴታ ያለበት መሆኑን ማወቅ አለበት፡፡
- ጽ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡–
- መረጃ መጠየቅ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0336610688 ወይም 0921037403 በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
- ጨረታውን የምናወዳድረው በሎት ስለሆነ በሎቱ ውስጥ ላሉ ዕቃዎች በሙሉ ዋጋ መሞላት አለበት ተጫራቹ ካልሞላ ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡
- የገዙትን የጨረታ ሰነድ ምንም ሳያስቀሩ የድርጅቱን ማህተም በማድረግ ላይተናነስ መመለስ ይኖርባችኋል።
- በዚሁ ጽ/ቤት ቀደም ሲል ለውድድር ተጋብዘው አሸናፊ ሆነው ለማቅረብ ፈቃደኛ ያልሆኑ ነጋዴዎችን በሙሉ የማናሳትፍ መሆኑን ማወቅ ይኖርባችኋል፡፡
በሰሜን ሸዋ ዞን የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት