Your cart is currently empty!
የቤት የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
Addis Zemen(Aug 31, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
የፍ/ባለመብት ወ/ሮ አየለች ሽፈራው እና የፍ/ባለዕዳ እነ ወ/ሮ ከፈኒ ሽፈራው መካከል ስላለው የፍርድ አፈጻጸም ጉዳይ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁጥር 146816 በ22/5/2016 ዓ/ም እና በኮ/መ/ቁ/02413 በ13/02/2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት በሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ፍርድ ለመፈጸም ይቻል ዘንድ ፍርድ ያረፈበት ቤት በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 የአዲስ አበባ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ቦሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በደብዳቤ ቁጥር አ/መ/ል/አስ/ቢ/ቦሌ/ቅ/ጽ/ቤት/0702/2017 ዓ.ም በሰጠው 3ገፅ ምላሽ ላይ በስኬች ወይም በንድፍ ተራ ቁጥር 1 በሚል የተገለጸውን ለፍ/ባለመበት እና ከተራ ቁጥር ከ1 እስከ 5 ለተጠቀሱት ለየ/ባለዕዳዎች ድርሻ የሆነውን የጨረታ መነሻ ዋጋ የሊዝ ግምት 4,239,990 (አራት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ብር) በቁጥር ቦሌ 12/55/3/6/54402/22 ስፋቱ 500 ካ.ሜ የሆነ ቤት በባለሙያ በ24/01/2017 ዓ/ም በቁጥር አአ/ መል/አስ/ቢ/ቦሌ/ቅ/ጽ/ቤት 0702/02/2017 ዓ.ም በተላከ ስኬች ላይ በተራ ቁጥር 1 ላይ ያለው የይዞታው ስፋት በሐራጅ የሚሸጠው 250 ካ/ሜ መሆኑ ይዞታው ምንም አይነት ግንባታ የሌለው ባዶ ቦታ ሆኖ የትራዛከሸን ታከስ ገዥ የሚከፍል መሆኑ ታውቆ መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ/ም በሐራጅ ይሸጣል፡፡ የተጫራቾች ምዝገባ 8፡30 ሰዓት ተጀምሮ የቀረቡ ተጫራቾች ተመዝግበው እንደተጠናቀቀ ወዲያውኑ ጨረታው የሚካሄድ ይሆናል፡፡
የሐራጁ ሽያጭ የሚካሄደው በፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍርድ አፈጻጸም ዳይሬክቶሬት የጨረታ አዳራሽ ውስጥ ሲሆን፣ ንብረቱን ተጫርተው ለመግዛት የሚፈልጉ ተጫራቾች ከጨረታው ቀደም ብሎ ባሉት አራት የሥራ ቀናቶች ውስጥ ባለመብቱ ለማስጎብኘት በሚመርጧቸው ሶስት የስራ ቀናት በፌ/ፍ/ቤቶች ፍርድ አፈፃፀም ዳይሬክቶሬት ሐራጅ ከፍል ድረስ ከጠዋቱ በ3፡30 ብቻ በመገኘትና ባለመብቱ በሚያቀርበው ትራንስፖርት ንብረቱን ባለበት ቦታ ድረስ በመውሰድ ለመጐብኘት የሚችሉ ሲሆን እያንዳንዱ ተጫራች በሚጫረትበት ወቅት የንብረቱን መነሻ ግምት 1/4 ኛውን በንግድ ባንክ በተረጋገጠ CPO ማስያዝ ይኖርበታል፡፡ ከ1/4ኛው አስበልጦም ሆነ አሳንሶ የሚያመጣ ተጫራች በጨረታው አይካፈልም፡፡ በጨረታው አሸናፊ የሆነው ግለሰብ አሸናፊ የሆነበትን ገንዘብ በአጠቃላይ ጨረታውን ካሸነፈበት ቀን ጀምሮ በፍ አፈ/ዳ/ ስም CPO በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ አሰርቶ ሙሉ ገንዘቡን በ15 ቀናት ውስጥ ገቢ ማድረግ አለበት በጨረታ አሸናፊ የሆነ በጨረታ ያሸነፈበትን ገንዘብ ገቢ ሳይደረግ ቀርቶ በቀጣይ ጨረታ ተደርጎ ጨረታው ከበፊቱ ጨረታው ቀንሶ ከተሸጠ ገዥው በልዩነት ተጠያቂ እንደሚሆን የፍአፈዳይሮክቶሬቱ ንብረቱን በህጋዊ መንገድ በሐራጅ ስለመሸጡ ለሚመለከተው አካል ማስረጃ ከመጻፍ ባለፈ ስም የማዛወር ግዴታ የሌለበት መሆኑን እንገልፃለን።
የፌዴራል ፍ/ቤቶች የፍርድ አፈፃፀም ጽ/ቤት