Your cart is currently empty!
በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን የሀ/ማ/ከ/ወ/ገ/ፅ/ቤት በወረዳው ለሚገኙ ጽ/ቤቶች ለ2018 በጀት ዓመት የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Sep 02, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን የሀ/ማ/ከ/ወ/ገ/ፅ/ቤት በወረዳው ለሚገኙ ጽ/ቤቶች ለ2018 በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡–
- የጽህፈት መሳሪያዎች
- የጽዳት ዕቃ
1. በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው እና የታደሰ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት በአቅራቢነት ማስረጃ ያላቸው
3. የግዥው መጠን ብር 200,000 / ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክርነት ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
5. የሚገዙ እቃዎችን አይነት ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ።
6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100/ አንድ መቶ ብር/ ብቻ በመከፈል ከፋይናንስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 2 ማግኘት ይችላሉ።
7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ለሚወዳደሩበት ለጽህፈት መሳሪያ 10,500/አስር ሺህ አምስት መቶ ብር ብቻ፣ ለፅዳት እቃ 4000/አራት ሺህ ብር ብቻ /በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲ.ፒ.ኦ/ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በመሂ 1 በመቁረጥ የመሂ 1 ኮፒ ተደርጎ ማስያዝ ይችላሉ።
8. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በሀ/ማ/ከ/ወ/ገ/ጽ/ቤት ግዥ /ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 6 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግዥ /ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 6 በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ቀን 4፡00 ሰዓት ይከፈታል ። 16ኛው ቀን በአል ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ታሽጎ በዚያው ቀን 4፡00 ሰአት ይከፈታል ።
10. ተጫራቹ ናሙና ለሚያስፈልጋቸው እቃዎች ጨረታው እስከሚዘጋበት እስከ 16ኛው ቀን 3፡30 ድረስ ናሙና ማቅረብ መቻል አለበት።
11. መ/ቤቱ ጨረታውን እንደአዋጭነቱ በተናጠል ወይም በጥቅል ሊሰጥ ይችላል።
12. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
13. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 6 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 011 619 0146/148 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።
አድራሻ፡– ከአዲስ አበባ 130 ኪ.ሜ ርቀት ወደ ደብረብርሃን 80 ኪ.ሜ ርቀት በሚወስደው አስፋልት ከሸኖ ከተማ አለፍ ብሎ ወደ ምስራቅ 39 ኪ.ሜ ገባ ብሎ እንገኛለን።
በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን የሀ/ማ/ከ/ወ/ገ/ ፅ/ቤት