Your cart is currently empty!
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን የጽሕፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃዎች፣ አይሲቲ እቃዎች እና ቶነሮች እንዲሁም የመኪና ጎማዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Sep 07, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ደ/አ/አ/ሪ/ግ/ጨ/001/2018
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን የጽሕፈት መሳሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃዎች፣ አይሲቲ እቃዎች እና ቶነሮች እንዲሁም የመኪና ጎማዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ምድብ |
ተ.ቁ |
የዕቃው ዓይነት |
የመዝጊያ ቀን እና ሰዓት |
የመክፈቻ ቀን እና ሰዓት |
የጨረታ ማስከበሪያ |
ሎት-1 እና ሎት2 |
1. |
የጽዳት ዕቃዎች (ሳሙና እና ሶፍት ወረቀት) |
መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት |
መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት |
50,000.00 |
2. |
የጽህፈት መሳሪያዎች |
መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት |
መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት |
100,000.00 |
|
ሎት-3 |
3. |
አይሲቲ እቃዎች እና ቶነሮች |
መስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት |
መስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት |
150,000.00 |
ሎት-4 |
4. |
የመኪና ጎማ |
መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት |
መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት |
150,000.00 |
1. ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራ የዘመኑን ግብር የተከፈለበት የንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለው በጨረታው መሳተፍ ይችላል፡፡
2. ተጫራቾች የመንግስት ድርጅቶች በሚያወጡት ጨረታ ላይ ለመሳተፍ እንዲችሉ በግዥ ኤጀንሲ ዌብሳይት ላይ የተመዘገቡ መሆኑን ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው፡፡
3. ተጫራቾች ለጨረታው ዝርዝር ሁኔታዎችን የሚገልጸውን ለሚወዳደሩበት የጨረታ ሰነድ መግዣ የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ) በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000173799946 (EEU-Southern Addis Ababa Region Customer Contribution) በማስገባት እና ደረሰኙን ይዞ በመምጣት ዘወትር በስራ ሰዓት ቅዳሜን እስከ 6፡00 ሰዓት ጨምሮ የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
4. አድራሻ፡– የቀድሞ ግሎባል ሆቴል ፊት ለፊት ማግባንዝ ህንጻ ላይ በሚገኘው ኢ/ኤ/አ ደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን 6ኛ ፎቅ ሰፕላይ ቼይን ንብረት እና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ፡፡
5. ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የሚያቀርቡት በባንክ በተረጋገጠ ቼከ/CPO/ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Bid Bond) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
6. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ ኦሪጅናል እና ኮፒ በማለት በተለያየ ፖስታ በማሸግ እና ሁለቱን በአንድ ትልቅ ፖስታ በማድረግ ጨረታ ቁጥር ደ/አ/አ/ሪ/ግ/ጨ/001/2018 የሚል ምልክት በማድረግ ሎቱን በመግለጽ ሎት-1 እና ሎት-2 እስከ መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ ሎት-3 እስከ መስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ እንዲሁም ሎት-4 እስከ መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ድረስ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
7. ጨረታው ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
8. ተቋሙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
9. ተጫራቾች መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር +251-114705377 መደወል ይችላሉ፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን ጽ/ቤት
አዲስ አበባ