Your cart is currently empty!
አልወሳኢል ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 05 ልዩ ቦታው ቡልጋሪያ ትራፊክ መብራት አካባቢ ያስገነባቸው አፓርትመንት ቤቶችና የንግድ ሱቆች፤ መተላለፊያዎችን፤ መስታወቶችን እና የውጪውን አካባቢዎች አጠቃላይ የፅዳት አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ድርጅቶች አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል
Addis Zemen(Sep 01, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
አጠቃላይ የህንፃ ፅዳት የጨረታ ማስታወቂያ
ማህበራችን አልወሳኢል ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 05 ልዩ ቦታው ቡልጋሪያ ትራፊክ መብራት አካባቢ ያስገነባቸው አፓርትመንት ቤቶችና የንግድ ሱቆች፤ መተላለፊያዎችን፤ መስታወቶችን እና የውጪውን አካባቢዎች አጠቃላይ የፅዳት አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ድርጅቶች አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
ስለሆነም በፅዳት አገልግሎት ስራ የተሰማራችሁና የወቅቱ ግብር የከፈላችሁ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 የስራ ቀናት ውስጥ የስራ ልምዳችሁንና ሌሎች ማስረጃዎቻችሁን በመያዝ በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ ሲሆን ጨረታው መስከረም 02 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ይከፈታል።
ለበለጠ መረጃ፡– በማህበሩ ጽ/ቤት ቡልጋሪያ ትራፊክ መብራት አካባቢ በአካል በመቅረብ ወይም፤
በስ.ቁ— 09 11-99-34-47 በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይቻላል።
ማሳሰቢያ፤ ማህበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
አልወሳኢል ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር