Your cart is currently empty!
ፀሀይ ኢንሹራንስ አ.ማ አዲስ አበባ ክልል ውስጥ ለሚገኙ ቅርንጫፍ ቢሮዎች የቅርንጫፉን መገኛ አቅጣጫ ለማመላከት የሚሰራ ዲጂታል ቦርድ በቋሚነት ውል ተዋውሎ ሊሰሩ የሚችሉ በዘርፉ ፍቃድ ካላቸው ተጫራቾች የአገልግሎት ግዢ መፈፀም ይፈልጋል
Reporter(Sep 07, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ግልፅ ጨረታ
ፀሀይ ኢንሹራንስ አ.ማ አዲስ አበባ ክልል ውስጥ ለሚገኙ ቅርንጫፍ ቢሮዎች የቅርንጫፉን መገኛ አቅጣጫ ለማመላከት የሚሰራ ዲጂታል ቦርድ በቋሚነት ውል ተዋውሎ ሊሰሩ የሚችሉ በዘርፉ ፍቃድ ካላቸው ተጫራቾች የአገልግሎት ግዢ መፈፀም ይፈልጋል::
ስለሆነም ማንኛውም መስፈርቱን የምታሟሉ እና በዘርፉ ፍቃድ ያላችሁ ተጫራቾች ከዚህ በታች በተገለፀው መስፈርት መስረት እንድትወዳደሩ ተጋብዛችኋል::
1. ተጫራቾች የሚሰጡት ዋጋ ዲጂታል ቦርዱን ሰርተው ከነመስቀያው ያጠቃለለ መሆን ይኖርበታል::
2. ተጫራቾች የ2017 ዓ.ም የታደስ ንግድ ፍቃድ እና የንግድ ምዝገባ ሰርተፊኬት የቫት እና ቲን ቁጥር ምዝገባ ሰርተፊኬት እና የታክስ ኪሊራንስ ሰርተፊኬት ማቅረብ ይጠበቅባችኋል::
3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 በመክፈል ከፋይናንስ እና አካውንቲንግ መምሪያ ከ 03/13/2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 10/01/2018 ዓ.ም ድረስ መግዛት ይችላሉ::
4. ጨረታው ከጳጉሜን 03/13/2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መስከረም 10/01/2018 ዓ.ም ድረስ አየር ላይ የሚቆይ ሲሆን ጨረታው በቀን 10/01/2018 ዓ.ም ጠዋት 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ ተጫራቾች(ህጋዊ ወኪሎቻቸው) በተገኙበት በዕለቱ 4፡30 በኩባንያው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል::
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid bond) 5,000.00 (አምስት ሺ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ክፍያ ማዘዣ ትዕዛዝ (cpo) ወይም ጨረታ ከተከፈተበት ዕለት አንስቶ ለ 90 ቀናት የሚቆይ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል::
6. ተጫራቾች ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነድ ኦሪጅናል እና ኮፒ በማዘጋጀት ዘውትር በስራ ሰዓት እሰከ 10/01/2018 ዓ.ም ጠዋት 4፡00 ሰዓት ድረስ በቀድሞው ብራስ ሆስፒታል ፊት ለፊት በሚገኘው ፀሀይ ኢንሹራንስ አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት 1ኛ ፎቅ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል::
ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ፀሀይ ኢንሹራንስ አ.ማ.
ስልክ +25111111970/0911394017
የሰው ሀብት እና ንብረት አስተዳደር መምሪያ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ