የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ሥርዓትን ተከትሎ ለኤሌክትሪካል እና መካኒካል ወ/ሾፕ የሚውሉ ግብዓቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen(Sep 25, 2025)

Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።

ጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር ኢኤስ/ፍፋግ/ግጨ-005/2018

ተቋማችን የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ሥርዓትን ተከትሎ ለኤሌክትሪካል እና መካኒካል ወ/ሾፕ የሚውሉ ግብዓቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

ተ.ቁ

የዕቃው ዓይነት

የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ (CPO)

የጨረታ መዝጊያ ቀን እና ሰዓት

የጨረታ መክፈቻ ቀን እና ሰዓት

1

ለኤሌክትሪካል እና መካኒካል ወ/ሾፕ የሚውሉ ግብዓቶች ግዥ

500,000.00 (አምስት መቶ ሺ)

መስከረም 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት

መስከረም 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት

  1. ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራ የዘመኑ ግብር የተከፈለበት የንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የታደሰ የታክስ ከሊራንስ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለው በጨረታው መሳተፍ ይችላል።
  2.  ተቋማችን አሌክትሮኒከስ ግዥ ሥርዓትን ተግባራዊ ማድረግ ስለጀመረ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች በሙሉ በተራ ቁጥር 1 ላይ የተዘረዘሩትን ሰነዶች በመያዝ ወደ ተቋማችን ቢሮ ሜክሲኮ ንብ ባንክ በሚገኝበት ዋናው መስሪያ ቤት 10ኛ ፎቅ ፍሊትና ፋሲሊቲ ግዥ ከፍል በአካል በመቅረብ መለያ ስም እና የሚስጥር ቁጥር ለመውሰድ መመዝገብ ይኖርባቸዋል።
  3. ተጫራቾች የሚስጥር ቁጥራቸውን ከወሰዱ በኋላ ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የኤሌክትሮኒክስ የጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000068699332 በመክፈል ባንክ የከፈሉበትን የከፍያ ሰነዱን ስካን በማድረግ misrakfan@gmail.com ወይም getv3010@gmail.com  በሚል ኢሜይል አድራሻ መላክ ይኖርባቸዋል።
  4. በመቀጠል በተቋሙ የዌብሳይት አድራሻ https://eeusrmvendorportal.ethiopianelectricutility.et/irj/portal ላይ በተሰጣቸው መለያ ስም እና የሚስጥር ቁጥር በመግባት ማግኘት ይችላሉ።
  5. የኤሌክትሮኒክስ የጨረታ ሰነድ ያገኘ ተጫራች የኤሌክትሮኒክስ ዘዴን በመጠቀም ምላሽ ለመስጠት ተቋማችን በሚያመቻቸው የስልጠና training orientation/ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ስልጠናውን በመውሰድ መሆን ይኖርበታል።
  6. አድራሻ፡- ሜክሲኮ ንብ ባንክ በሚገኝበት ዋናው መስሪያ ቤት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋናው መስሪያ ቤት 10ኛ ፎቅ ፍሊትና ፋሲሊቲ ግዥ ከፍል ስልክ ቁጥር 011 26 6605/ 011 156-0148
  7. ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና <> በሚል መሆን ይኖርበታል !
  8. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን የኤሌክትሮኒከስ ግዢ የምላሽ አሰጣጥ ስርአትን በመከተል ከላይ እስከ ተጠቀሰው ቀን እና ሰዓት መሆን ይኖርባቸዋል፣
  9. ጨረታው ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ቀን 8፡30 ሰዓት ላይ የኤሌክትሮኒክስ የግዢ ስርአትን በመከተል በኦንላይን ስለሚሆን በተራ ቁጥር 4 በተገለጸው መሰረት በኦን ላይን ይሆናል።
  10. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ኦሪጅናል እና ናሙና ለሚያስፈልጋቸው ዕቃዎችናሙናውን ጨረታው በሚዘጋበት ቀንና ሰዓት ንብ ባንከ 10ኛ ፎቅ ፍሊትና ፋሲሊቲ ግዥ ከፍል በአካል ማቅረብ አለባቸው።
  11. ተቋሙ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *