Your cart is currently empty!
በልደታ ክ/ከተማ ትም/ፅ/ቤት በወረዳ 10 ስር የሚገኘው የፍሬህይወት ቁ.1 ቅድመ አንደኛ አንደኛና መካከለኛ ደ/ት/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የሚፈልጋቸውን የትምህርት ቁሳቁሶችና ሌሎች ግብዓቶችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Addis Lessan(Oct 11, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቅያ
የግዥ መለያ ቁጥር 01/2018 ዓ.ም
በልደታ ክ/ከተማ ትም/ፅ/ቤት በወረዳ 10 ስር የሚገኘው የፍሬህይወት ቁ.1 ቅድመ አንደኛ አንደኛና መካከለኛ ደ/ት/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የሚፈልጋቸውን የትምህርት ቁሳቁሶችና ሌሎች ግብዓቶችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በዚሁም መሰረት፦
- ሎት 1 የደንብ ልብስ ግዢ የጨረታ ማስከበሪያ 16,500.00
- ሎት 2 የደንብ ልብስ ስፌት የጨረታ ማስከበሪያ 3,000.00
- ሎት 3 የፅህፈት መሣርያና አላቂ የቢሮ ዕቃዎች ግዢ የጨረታ ማስከበሪያ 16,500.00
- ሎት 4 ህትመት የጨረታ ማስከበሪያ 1,950.00
- ሎት 5 ለአላቂ የህክምና ዕቃዎች ግዢ የጨረታ ማስከበሪያ 363.00
- ሎት 6 ለአላቂ የትምህርት ዕቃዎች ግዢ የጨረታ ማስከበሪያ 2,513.00
- ሎት 7 አላቂ የፅዳት ዕቃዎች ግዢ የጨረታ ማስከበሪያ 18,000.00
- ሎት 8, ልዩ ልዩ መሳሪያዎች ግዢ የጨረታ ማስከበሪያ 375.00
- ሎት 9. ለፕላንት ማሽነሪ ዕቃዎች ግዢ የጨረታ ማስከበሪያ 1500.00
- ሎት 10 ለፕላንት ማሽነሪ ዕቃዎች ጥገና የጨረታ ማስከበሪያ 1500.00
- ሎት 11 ለህንፃ ቁሳቁስ ተገጣጣሚ ጥገና የጨረታ ማስከበሪያ 1500.00
- ሎት 12 ለፕላንት ማሽነሪ ቋሚ ዕቃዎች በር የጨረታ ማስከበሪያ 4,500.00
- ሎት 13 ለህንፃ ቁሳቁስ ቋሚ ዕቃዎች ግዢ የጨረታ ማስከበሪያ 3,000.00
መስሪያ ቤቱ ባወጣው ግልፅ ጨረታ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ። በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎት ላላቸው ተጫራጮች የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ በመንግስን አስ ኤጀንሲ ድረ ገጽ በአቅራቢዎች ምዝገባ ዝርዝር የተመዘገቡ የተንና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ በተወዳደሩበት ሎት የተጠቀሰውን የጨረታ ማስከበሪያ በትምህርት ቤቱ ስም በማሰራት ከጨረታ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- የጨረታ አሸናፊ 10% የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማስያዝ ይኖርበታል።
- ተጫራቾች በአዲስ ልሳን ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት አንስቶ በተከታታይ አስር የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል በፍሬህይወት ቁ,1 ቅድመ አንደኛ፤ አንደኛና መካከለኛ ደ/ት/ቤት በቢሮ ቁጥር 7 በመምጣት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይቻላል።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቅያው ከወጣበት ዕለት ጀምሮ በተከታታይ 10 የሥራ ቀናት በፍሬህይወት ቁ.1 ቅድመ አንደኛ፡ አንደኛና መካከለኛ ደ/ት/ቤት ሁለተኛው ጊቢ ፋይናንስ ቢሮ በረንዳ ላይ ለጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታውን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ11ኛው ቀን ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዛኑ ቀን ከቀኑ 4፡30 ሰዓት የፍሬህይወት ቁ.1 ቅድመ አንደኛ፤ አንደኛና መካከለኛ ደት ቤት ይከፈታል። የመከፈቻው ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት ታሽጎ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሣጥኑ ከመከፈቱ በፊት የተወዳደሩባቸውን ሎት 1፣ ሎት 3፣ ሎት 4፣ ሎት 5፣ ሎት 6፣ ሎት 7፣ ሎት 8 እና ሎት 9 ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ናሙና ማቅረብ የማይችሏቸውን ቋሚ ዕቃዎችን ሎት 12 እና ሎት 13 በፎቶ ግራፍ የተደገፈ ናሙና (በስፔሲፊኬሽን መሰረት) ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ት/ቤቱ ጨረታውን የመክፈት መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ዕቃዎች ለእያንዳንዱ ሻት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።
- የዘገየ ጨረታና በጨረታ መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም።
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፏቸውን ዕቃዎች በራሣቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈፃሚው መሥሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ት/ቤቱ ዕቃዎችን የመቀነስ ወይም የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው።
- አድራሻ፡- በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ሜክሲኮ የፍሬህይወት ቁ.1 ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ ደ/ት/ቤት በመከላከያ ኢንጅነሪንግ (ሜቴክ) ገባ ብሎ ሌጆ አልሙኒየም አጠገብ ነው
- ስልክ 011 515 7818 ወይም 011 558 3860 የፍሬህይወት ቁı ቅድመ አንደኛ፤ አንደኛና መካከለኛ ደ/ት/ቤት
በአዲስ አበባ አስተዳደር ት/ቢሮ በልደታ ክ/ከተማ ትም/ጽ/ቤት
የፍሬህይወት ቁ. 1 ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት
cttx Advertising and Promotion cttx, cttx Building and Finishing Materials cttx, cttx Cleaning and Janitorial Equipment and Service cttx, cttx Computer and Accessories cttx, cttx Construction and Water Works cttx, cttx Construction Machinery and Equipment cttx, cttx Education and Training cttx, cttx Electrical, cttx Equipment and Accessories cttx, cttx Health Care, cttx Health Related Services and Materials cttx, cttx Industrial Machinery Provision and Installation cttx, cttx IT and Telecom cttx, cttx Machinery cttx, cttx Maintenance and Repair cttx, cttx Materials cttx, cttx Office Machines and Accessories cttx, cttx Office Machines and Computers cttx, cttx Office Supplies and Services cttx, cttx Others cttx, cttx Printed Advertising Materials cttx, cttx Printing and Publishing cttx, cttx Shoes and Other Leather Products cttx, cttx Stationery cttx, cttx Textile, Electromechanical and Electronics cttx, Garment and Leather cttx, Garments and Uniforms cttx, Medical Industry cttx