Your cart is currently empty!
በመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን የኤም ኤን ኤስ ማኑፋክቸሪንግ እና ትሬዲንግ እስከ 1,500 ለሚደርሱ ለሰራተኞቻችን የምግብ አገልግሎት የሚሰጥ አሽናፊ የሆነዉን አወዳድሮ ለአሸናፊው ውል መያዝ ይፈልጋል
Reporter(Oct 12, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
መከላከያ ሰራዊት ፋዉንዴሽን ኤም ኤን ኤስ ማኑፋክቸሪንግ እና ትሬዲንግ
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሰራተኞች የምግብ አገልግሎት ማቅረብ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር PUR 002/2018
በመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን የኤም ኤን ኤስ ማኑፋክቸሪንግ እና ትሬዲንግ የተለያዩ ጨርቃጨርቅና ፎጣዎችን አምራች ድርጅት ሲሆን እስከ 1,500 ለሚደርሱ ለሰራተኞቻችን የምግብ አገልግሎት የሚሰጥ አሽናፊ የሆነዉን አወዳድሮ ለአሸናፊው ውል መያዝ ይፈልጋል። ድርጅቱ ዉሃ መብራት የቤት ኪራይ እና አንዳንድ ማብሰያ እቃዎችን ይሸፍናል።
በዚህም መሰረት ህጋዊ ተጫራቾች የሚከተሉትን የጨረታ መስፈርቶች በማሟላት እንድትወዳደሩ እየጠየቅን ለበለጠ ማብራሪያ ከታች በሚገኘው የስልክ አድራሻ በመጠየቅ መረዳት ይችላሉ።
| የአልግሎት አይነት | የጨረታው ሰነድ ግዥና መመዝገቢያ ቀን | የጨረታው መክፈቻ ቀንና ሰዓት | 
| ለፋብሪካው ሰራተኞች የምግብ አገልግሎት መስጠት | ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት | 
 | 
ስለሆነም፡–
1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፊቃድ ያላቸው ሆኖ ኮፒውን ማቅረብ የሚችሉ፣
2. የጨረታ ማስከበሪያ 100,000 ብር በመከላከያ ሰራዊት ፋውንዴሽን የኤም ኤን ኤስ ማኑፋክቸሪንግ ትሬዲንግ ስም የተዘጋጀ በባንክ በተመሰከረለት የባንክ ቼክ (CPO) ማቅረብ የሚችሉ፣
3. የታክስ ኪሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ፣
4. የ500,000 ብር በየስድስት ወራት የሚታደስ ቼክ ማቅረብ የሚችል፣
5. እውቅና ካለው መስሪያ ቤት በምግብ ስራ የምስክር ወረቀት ያለው፤
6. ከዚህ በፊት ቢያንስ 6 ዓመት በምግብ አገልግሎት ላይ የፈረቃ ሰራተኞች ካላቸው ታዋቂ ድርጅቶች ጋር የሰራ፣
7. ከዚህ በፊት ከሰራባቸው ቦታዎች የመልካም ስራ ምስጋና ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፤
8. የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት /VAT/ ማቅረብ የሚችል፣
9. የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /TIN Number/ ቁጥር ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ፣
10. የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፤
11. ተጫራቾች በየቀኑ እስከ 1,500 ሰራተኞች መመገብ የሚችል አቅም ያላቸው፣
12. ተጫራቾች የጨረታውን ሙሉ ዝርዝር የያዘ ሰነድ የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አስር ተከታታይ የስራ ቀናት ለገጣፎ ከሚገኘው ድርጅታችን ከፋይናንስ መምሪያ ቢሮ ቀርበው መግዛት ይችላሉ፤
13. ተጫራቾች በጨረታው መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ባይገኙ የጨረታውን መክፈት ሂደት አያስተጓጉልም። ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ
ስ.ቁ፡– 0910 744 45 ፣ 09 13 17 69 75፣ 09 12 35 51 48፣ 09 61 02 01 60 እና 09 11 96 80 58