Your cart is currently empty!
በኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ፍንፍኔ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የተለያዩ የኮምፒውተር፣ የኢንተርኔት፣ የፎቶ ኮፒ ማሽኖችን የጥገና አገልግሎትን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Oct 18, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ
የጨረታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን የተለያዩ የኮምፒውተር፣ የኢንተርኔት፣ የፎቶ ኮፒ ማሽኖችን የጥገና አገልግሎትን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም ተጫራቾች በጨረታው ላይ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች ተዘረዘሩትን መስፈርት ማሟላት አለባቸው።
1. በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው እና ኮፒውን ማቅረብ የሚችሉ፡፡
2. የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) እና የሥራ መለያ ቁጥር ቲን ቁጥር ያላቸውና ኮፒውን ማቅረብ የሚችሉ።
3. ተጫራቾች በጨረታ ላይ ለመሳተፍ የሚያስችል ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
4. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ካቀረቡት ጠቅላላ ዋጋ 5% በባንክ በተረጋገጠ በሲፒኦ በድርጅቱ ስም ማስያዝ ይኖርበታል፡፡ የጨረታ ሠነዱን ላምበረት ከቴሌ ጀርባ ከሚገኘው ቅርንጫፍ ጽ/ቤታችን ከሰኞ እስከ ቅዳሜ 6፡00 በሥራ ሰዓት በማይመለስ 300.00 (ሶሰት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሠነዱን መግዛት የሚችሉ መሆኑን እየገለፅን፣ ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን በ16ኛው ቀን ዕሁድ ወይም የህዝባዊ በዓል ላይ ከዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያው ዕለት ከጠዋቱ በ4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው የሚከፈት መሆኑን እየገለፅን፣ ድርጅታችን የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0985 380 095 /0945 780 983 ደውሉ መጠየቅ ይቻላል፡፡
በኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ፍንፍኔ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት