Your cart is currently empty!
የቦታው ስፋቱ በካርታቸው መሰረት 480 ካ/ሜ የቤት የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
Addis Zemen(Oct 18, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
በፍ/ባለመብት እነ ናትናኤል ዮሴፍ እና በፍ/ባለዕዳ አቶ አዳሙ አየነው መካከል ስላለው የፍርድ አፈጻጸም ጉዳይ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁጥር/315157 በሚያዝያ 1 ቀን 2016 ዓ/ም በ13/3/2017 ዓ/ም እና በኮ/መ/ቁ/322994 በ04/6/2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት በሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ፍርድ ያረፈበት ቤት በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 07 የቤት ቁጥር 406 የሆነውና የፍ ባለዕዳ ድርሻ የሆነው ይዞታ የሐራጅ መነሻ ዋጋ ብር 4,213,160 (አራት ሚሊዮን ሁለት መቶ አስራ ሦስት ሺህ አንድ መቶ ስልሳ ብር) ፍርድ ያረፈበት ቤት ቦሌ7/22/8/8/7022/311398/187014/02 ወረዳ 7 ብሎክ 69 ፓርሴል 93 የቦታው ስፋቱ በካርታቸው መሰረት 480 ካ/ሜ በእነ ወለላ አሊ በላቸው ስም ከተጠቀሰው የካርታ ይዞታ ላይ ተከፍሎ 85 ካ/ሜ በሽያጭ የተላለፈ ሲሆን በአክል በልኬት የተወሰደ የይዞታው ስፋት 106 ካ/ሜ ያህል መሆኑ አጠቃላይ ስፋት ከነቤዝመቱ 87 ካ/ሜ መሆኑ ቤቱ በብሎኬት የተሰራ መሆኑ በካ/ቁ/ቦሌ7/22/8/7022/311398/187014/02 ወረዳ 7 ብሎክ ቁጥር 69 ፓርሴል 93 የቦታው ስፋቱ በካርታቸው መሰረት 480 ካ/ሜ በእነ ወ/ሮ ወለላ አሊ በላቸው ስም ከተጠቀሰው የካርታ ይዞታ ላይ ተከፍሎ የተሰጠው 85 ካ/ሜ ስም ለማዞር በሽያጭ የተላለፈው ይዞታ በግዥ ስም ካርታ ሲሰራ መሆኑ ሆኖ የትራዛክሽን ታክስ ገዥ የሚከፍል መሆኑ ታውቆ ህዳር 11 ቀን 2018 ዓ.ም በሐራጅ ይሸጣል። የተጫራቾች ምዝገባ 4፡00 ሰዓት ተጀምሮ የቀረበ ተጫራቾች ተመዝግበው እንደተጠናቀቀ ወዲያውኑ ጨረታው የሚካሄድ ይሆናል።
የሐራጁ ሽያጭ የሚካሄደው በፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍርድ አፈጻጸም ጽ/ቤት የጨረታ አዳራሽ ውስጥ ሲሆን፣ ንብረቱን ተጫርተው ለመግዛት የሚፈልጉ ተጫራቾች ከጨረታው ቀደም ብሎ ባሉት አራት የሥራ ቀናቶች ውስጥ ባለመብቱ ለማስጎብኘት በሚመርጧቸው ሶስት የስራ ቀናት በፌ/ፍ/ቤቶች ፍርድ አፈፃፀም ጽ/ቤት ሐራጅ ክፍል ድረስ ከጠዋቱ በ3፡30 ብቻ በመገኘትና ባለመብቱ በሚያቀርበው ትራንስፖርት ንብረቱን ባለበት ቦታ ድረስ በመውሰድ ለመጐብኘት የሚችሉ ሲሆን እያንዳንዱ ተጫራች በሚጫረትበት ወቅት የንብረቱን መነሻ ግምት 1/4 ኛውን በንግድ ባንክ በተረጋገጠ CPO ማስያዝ ይኖርበታል። ከ1/4ኛ አስበልጦም ሆነ አሳንሶ የሚመጣ ተጫራች በጨረታው አይካፈልም። በጨረታው አሸናፊ የሆነው ግለሰብ አሸናፊ የሆነበትን ገንዘብ በአጠቃላይ ጨረታውን ከአሸነፈበት ቀን ጀምሮ በፍ/አፈ/ጽ/ቤት ስም CPO አሰርቶ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ ሙሉ ገንዘቡን በ15 ቀናት ውስጥ ገቢ ማድረግ አለበት። በጨረታ አሸናፊ የሆነ በጨረታ ያሸነፈበትን ገንዘብ ገቢ ሳይደረግ ቀርቶ በቀጣይ ጨረታ ተደርጎ ጨረታው ከበፊቱ ጨረታው ቀንሶ ከተሸጠ ገዥው በልዩነት ተጠያቂ እንደሚሆን የፍ/አፈ/ጽ/ቤት ንብረቱን በህጋዊ መንገድ በሐራጅ ስለመሸጡ ለሚመለከተው አካል ማስረጃ ከመጻፍ ባለፈ ስም የማዛወር ግዴታ የሌለበት መሆኑን እንገልፃለን።
የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍርድ አፈፃፀም ጽ/ቤት