Your cart is currently empty!
የሶዶ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የቤት ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ አውጥቷል
Yedebub Nigat(Oct 18, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የቤት ሸያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
በአፈፃፀም ከሣሾች እነ ታደለች ጋንታ እና በአፈፃፀም ተከሣሽ አቶ ሰለሞን ጋንታ መካከል ባለው የአፈፃፀም ውርስ ንብረት ክስ መነሻ በሶዶ ከተማ መርካቶ ይሹዋ ቀበሌ ውስጥ በሟች አቶ ጋንታ ጋኔቦ ስም ተመዝግቦ የሚገኘውን ይዞታና በላዩ ላይ ያለውን መኖሪያ ቤት በሳይት ቁጥር ሽ/1061/04 የቦታ ስፋት 355.8 የሰፈረ የመሐንዲስ ግምት መነሻ ብር 5,145,437.50/አምስት ሚሊዮን አንድ መቶ አርባ አምስት ሺህ አራት መቶ ሰላሳ ሰባት ብር ከ50/100 ሳንቲም/ ስለሆነ ለመጫረት የሚፈልግ ግለሰብ ህዳር 01/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 6፡00 ሰዓት ድረስ ባለው ጊዜ እንዲጫረት ፍ/ቤቱ አዟል፡፡
የሶዶ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት