Your cart is currently empty!
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን በገ/ጉ/ወ/ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለወረዳው ጤና ጽ/ቤት በዋን ዋሽ በጀት ለኢንጌ፣ ለጅማ ወለኔ፣ ለገሬኖና ለአበዘት ጤና ጣቢያ አመድ መቅበሪያና ለአበዘት ጤና ጣቢያ የደረቅ ቆሻሻ ማቃጠያ ስራ ለማሰራት በግልጽ ጨረታ ለመጀመሪያ ጊዜ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል
Addis Zemen(Oct 27, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ ሀገር አቀፍ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር GGWW/002/2018
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን በገ/ጉ/ወ/ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለወረዳው ጤና ጽ/ቤት በዋን ዋሽ በጀት ለኢንጌ፣ ለጅማ ወለኔ፣ ለገሬኖና ለአበዘት ጤና ጣቢያ አመድ መቅበሪያና ለአበዘት ጤና ጣቢያ የደረቅ ቆሻሻ ማቃጠያ ስራ ለማሰራት በግልጽ ጨረታ ለመጀመሪያ ጊዜ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች፡–
1. የዘመኑ ንግድ ፍቃድ ያሳደሱ፣ የቫት እና ቲን ነምበር ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
2. በጨረታው ለመወዳዳር የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች የሚገዙት ጨረታ ሰነዱን ጠቅሰው በማመልከቻ ሲጠይቁ ተወካዮች ከሆኑ ከድርጅቱ ሕጋዊ ውክልና ይዘው መምጣት አለባቸው።
3. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21ኛው ተከታታይ ቀናት እስከ 8፡00 ሰዓት ድረስ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል የጨረታውን ሰነድ መሀልአምባ ከተማ ገ/ጉ/ወ/ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ድረስ በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ።
4. የመወዳደሪያ ደረጃቸውም GC ደረጃ 7 እና ከዚያ በላይ የሆኑ ተቋራጮች።
5. የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ብቻ ብር 100,000 (አንድ መቶ ሺህ ብር) ለሁለቱም ሰነዶች በገ/ጉ/ወ/ወ/ፋይናንስ ጽ/ቤት ስም ማሰራት አለባቸው።
6. ተጫራቾች የጨረታውን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ዶክመንት ሀ/ ለቴክኒካል ዶክመንት አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ፎቶ ኮፒ በማድረግ ቴክኒካል በሚል በመለየት ለ/ ለፋይናንሻል ዶከመንት አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ፎቶ ኮፒ በማድረግ ፋይናንሻል በሚል በመለየት በሰም በማሸግ ከላይ በተጠቀሰው የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ/ ከባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከቴክኒካል ኦርጅናል ዶክመንቱ ጋር በማድረግ በሰም በማሸግ ቴክኒካል ዶክመንት በሚል በመለት ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት 21(ሃያ አንድ) ተከታታይ ቀናት መሀልአምባ የገ/ጉ/ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር-03 ድረስ በመምጣት ለጨረታ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
7. የጨረታው ሰነድ በ21ኛው ተከታታይ ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ይታሽጋል። ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
9. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማሳሰቢያ ፡–
1. በአፈፃፀም ምክንያት ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ድርጅቶች መወዳደር አይችሉም።
2. በወረዳው ውስጥ ፕሮጀክት ይዞ ሥራውን ያልጨረሰ ተጫራች መወዳደር አይችልም።
3.ተጫራቾች ሰነድ ለመግዛት ሲመጡ ከአሰሪው መስሪያ ቤት የሳይት ምልከታ ማየታቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉና መሆን አለባቸው።
4. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ወይም ቅዳሜ ና እሁድ ከሆነ ወደሚቀጥለው የሥራ ቀን ይዘዋወራል።
ለበለጠመረጃ፡– የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ
ስልክ ቁጥር፡-011 336 0162/46 ይደውሉ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን የገ/ጉ/ወ/ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት