በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኤቨንት ኦርጋናይዘር በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen(Oct 28, 2025)

ከስር የተቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ። Please read the detailed instructions below.

የግዥ ጨረታ ማስታወቂያ /በድጋሚ የወጣ/

የጨረታ ቁጥር፡.... 003/2018

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ኤቨንት ኦርጋናይዘር በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

 ስለሆነም፡

  1. ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን አለባቸው።
  2. ተጫራቾች የቫት ተመዝጋቢ ሆነው ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉና መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር/ ያላቸው መሆን አለባቸው።
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ CPO ብር 75,000 /ሰባ አምስት ሺህ ብር/ ማስያዝ አለባቸው።
  4. ተጫራቾች ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል 5 ኪሎ ከሚገኘው ስፖርት ኮሚሽን ህንፃ 6 ፎቅ ግዢና ንብረት አስተዳደር ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ቢሮ በመቅረብ እስከ 10ኛው ቀን ድረስ መውሰድ ይችላሉ።
  5. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ቴከኒካል እና ፋይናንሻል ዋናውን እና ኮፒ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 11ኛው የስራ ቀን 400 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  6. ጨረታው የሚዘጋበት ቀን የጨረታ ማስታወቂያው በወጣ 11ኛው የስራ ቀን 400 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን 430 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመ/ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል። ሆኖም ግን የተጫራቾች አለመገኘት ጨረታውን ከመከፈት አያግደውም።
  7. ዘግይቶ የመጣ የጨረታ ፖስታ ተቀባይነት የለውም።
  8. ቢሮው ጨረታውን በከፊልም ይሁን ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ፡አምስት ኪሎ ብሔራዊ ሙዚየም ጀርባ የስፖርት ኮሚሽን ህንፃ 6 ፎቅ

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡– 011-140-7110

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *