Your cart is currently empty!
ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያ የፀጉር ቅባት፣ የልብስ ሣሙና እና የአልትራሳውንድ መሳሪያ መግዛት ይፈልጋል
Reporter(Oct 29, 2025)
ከስር የተቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ። Please read the detailed instructions below.
የጨረታ ቁጥር GNE-Procurement of (Hair oil, laundry soap and Ultrasound Machine):፡30/2025
ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያ መንግሥታዊ ያልሆነ ለትርፍ ያልተቋቋመ የውጭ በጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን መንግሥት ባወጣው የዳግም ምዝገባ ሥርዓት አጠናቆ በሰርተፊኬት ቁጥር 1135 በመመዝገብ በመላው ኢትዮጵያ በበጐ አድራጐት ሥራ ላይ (ንዲቀሳቀስ የተፈቀደለት ድርጅት ነው፡: በዚሁም መሠረት ድርጅቱ በሚከተሉት መደቦች ማለትም ከወይራ የተዘጋጀ የፀጉር ቅባት 397 gram ግዢ (በመደብ-1)፣ የልብስ ሣሙና (250 gm) ግዢ (በመደብ-2) እና የአልትራሳውንድ መሳሪያ ግዢ (በመደብ-3) በግልፅ ጨረታ ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያ በኘሮጀክቱ ለሚገኙ ለፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች እና ለጤና ጣቢያ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የተጠቀሱትን መስፈርቶች የምታሟሉ ህጋዊ ተጫራቾች እንድትሣተፉ ይጋብዛል።
ስለዚህ ግዢው ከዚህ በታች በሰንጠረዡ ውስጥ የተዘረዘሩትን መደቦችን ሁሉ የሚመለከት ይሆናል።
|
ተ.ቁ |
ዝርዝር/ Descriptions |
የዝርዝር መግለጫ/Specifications |
መለኪያ/ Measurement |
ብዛት/ Qty |
|
መደብ -1 |
ከወይራ የተዘጋጀ (ጭቃ ቅባት) ፈሣሽ ያልሆነ 1ኛ ደረጃ የፀጉር ቅባት Semi-solid, olive oil–based hair conditioning and styling pomade. |
397 gram |
በቁጥር |
5042 |
|
መደብ -2 |
የልብስ ሣሙና |
250 gm |
በቁጥር |
46,772 |
መደብ -3
1. የአልትራሳውንድ መሳሪያ (Ultrasound Machine) ዝርዝር መግለጫ / Specification Table
|
ULTRASOUND WITH TWO PROBES (2) |
መለክያ UOM |
ብዛት/ QTY |
|
|
Minimum Requirement |
Parameter
|
በቁጥር |
ሁለት(2) |
|
Clinical Purpose/Description: |
A Portable laptop type and detachable diagnostic imaging ultrasound used to see internal body structure in Abdomen, Obstetrics, Gynecological, Vascular, Musculoskeletal, small part(thyroid, breast), pediatrics and neonatal
|
||
ስለዚህ የሚከተለውን የጨረታውን መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾች እንዲወዳደሩ ይጋብዛል።
1. ተወዳዳሪዎች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/፣የዘመኑን ግብር ስለመክፈላቸው ማረጋገጫ /ክሊራንስ/፣ እና የተጨማሪ እእሴት ታክስ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራቾች እእነዚህን እእ“ ሌሎች ተያያዥነት ያላቸውን ማስረጃዎች ኮፒ በማድረግ በጀርባው ፊርማና ማህተም በማድረግ በማጫረቻ ሰነዳቸው ለይ ማካተት ይኖርባቸዋል።
2. ጨረታው በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ(7) ለስምንት ተከታታ የሥራ ቀናት ማለትም ጥቅምት 19/2018 እስከከ ጥቅምት 27/2018 በአየር ላይ ከቆየ በኋላ በ7ኛው ቀን ማለትም ጥቅምት 27/2018 ጠዋት 4፡00 ሠዓት ተዘግቶ በዛው ዕለት በ4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያ ልደታ ፕሮጀክት (ኮሪያ ት/ቤት በመባል የሚታወቀው) ከልደታ ቤ/ክ በስተጀርባ ባለው አዳራሽ ይከፈታል።
3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ከቀረበው ጠቅላላ ዋጋ 2% በባንክ በተመሰከረ ሲ.ፒ.ኦ ብቻ በድርጅቱ ስም በማሰራት ከጨረታ ዶክመንቱ ጋር በማያያዝ ለዚሁ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
4. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን ማለትም ቴክንካል ኦርጅናል እና ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሻል ኦርጅናል እና ኮፒ ሰነዳቸውን ለየብቻ በመለየት በሁለት ፖስታታበታሸገ ኤንቨሎፕ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
5. ተጫራቾች ዕቃውን የሚያቀርቡበት ጊዜ/Delivery time ውል ከተያዘበት ቀን ጀምሮ 1ዐ/አሥር ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ይሆናል።
6. ዕቃውን ማለትም ከወይራ የተዘጋጀ የፀጉር ቅባት 397 gram፣የልብስ ሣሙና (250 gm) /አልትራሳዉንድ መሳሪያውን ማስረከብያ በሚገኙበት አድራሻ (አንጐለላ እና ወልቂጤ) ይሆናል።
7. ተጫራቾች ሰነዱን ከጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያ ዋናው መ/ቤታችን በጋዜጣው ላይ በተጠቀሱት ቀናት መሰረት ከጠዋት 2፡30 ሰዓት እስከ ቀኑ 6፡00 ሰዓት እና ከሰዓት በኋላ 7፡00 ሰዓት አስከ 10፡00 የሚገኙ ይሆናል፡፡ የጨረታ ሰነዱን ልደታታክ/ከተማ ባልቻ ሆስፒታል ጀርባ አህመድ የገበያ ማዕከል 5ኛ ፎቅ በሚገኘው ከዋናው መ/ቤታችን በሥራ ሰዓት የማይመለስ ብር 600.00 /ስድስት መቶ ብር/ በመክፈል ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያ ፋይናንስ ክፍል መውሰድ ይችላሉ፡፡
8. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ቁሣቁሶች ከአልትራሣውንድ በስተቀር ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
9. ትራንስፖርት ኘሮጀክቶቹ በሚገኙበት አድራሻ (አንጐለላ እና ወልቂጤ) ድረስ በተጫራቾች የሚሸፈን ይሆናል፡፡
10. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሣሰቢያ፡–
1ኛ. አድራሻ – ሰነዱ የሚሸጥበት ዋናው መ/ቤት ባልቻ ሆስፒታል ጀርባ አህመድ የገበያ ማዕከል 5ኛ ፎቅ
2ኛ. አድራሻ – ጨረታው የሚከፈትበት እና ናሙና የሚሰጥበት ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያ ልደታ ፕሮጀክት (ኮሪያ ት/ቤት በመባል የሚታወቀው) ከልደታ ቤ/ክ በስተጀርባ በሚገኘው አዳራሽ ይሆናል፡፡
3ኛ. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ናሙና ጨረታው ከተከፈተ ጀምሮ በ5(አምስት) የሥራ ቀናት ውስጥ መውሰድ አለባቸው። ጨረታው ከተከፈተ አምስት የሥራ ቀናት በኋላ ድርጅቱ ለናሙናው ተጠያቂ አይሆንም።
ለበለጠ መረጃ፡ በስልክ ቁጥር +251-11 557 8614,+251-11 557 5889