ኢንክሉሲቭ ኤንድ አክሰሰብል ፎር ዲሴቢሊቲ እ.ኤ.አ ከጃንዋሪ 1 እስከ ዲሴምበር 31፣ 2025 እ.ኤ.አ ያለውን ሂሳብ በውጪ ኦዲተሮች ማስመርመር ይፈልጋል


Addis Zemen(Feb 01, 2026)

የኦዲት ሥራ ማስታወቂያ

ኢንክሉሲቭ ኤንድ አክሰሰብል ፎር ዲሴቢሊቲ እ.ኤ.አ ከጃንዋሪ 1 እስከ ዲሴምበር 31፣ 2025 እ.ኤ.አ ያለውን ሂሳብ በውጪ ኦዲተሮች ማስመርመር ይፈልጋል።

በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ የኦዲት ድርጅቶች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

1/ የ2018 ዓ/ም የታደሰ የንግድ ፍቃድ

2/ በህጋዊነት የምትታወቁና በመንግስት የተመዘገባችሁ

3/ የሂሳብ ምርመራ በቂ ባለሙያና የስራ ልምድ ያላችሁ

4/ የታክስ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላችሁ

5/ የዘመኑን ግብር ለመክፈላችሁ ማረጋገጫ ማቅረብ የምትችሉ።

ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች ለአገልግሎቱ የምትጠይቁትን ክፍያ፣ የሚከናወነውን የኦዲት ስራ ዝርዝርና ስራውን ሰርቶ ለማጠናቀቅ የሚወስደውን ጊዜ በመግለጽ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 7 ተከታታይ የስራ ቀናት ከታች በተቀመጠው አድራሻ በመቅረብ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

አድራሻ፡ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ከኦሮሚያ ፍርድ ቤት ከፍ ብሎ

ለበለጠ መረጃ፡ ስልክ ቁጥር 09 34 47 21 71
ኢንክሉሲቭ ኤንድ አክሰሰብል ፎር ዲሴቢሊቲ


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *