Your cart is currently empty!
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ በፋብሪካዉ አገልግሎት የሚዉል Laminated Poly Propylene PPC Cement Bags አቅራቢዎችን በግል በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Feb 04, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
የሀገር ውስጥ ጨረታ ቁጥር ሙሲፋ/09/2018
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ በፋብሪካዉ አገልግሎት የሚዉል Laminated Poly Propylene PPC Cement Bags ብዛት በቁጥር 13,000,000 (አስራ ሶስት ሚሊዮን) አቅራቢዎችን በግል በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ ሕጋዊ የንግድ ምዝገባና የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉና የተጨማሪ እሴት ታክስ እና ታክስ ከፋይ ተመዝጋቢ የሆኑ የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ኮፒ በመያዝ ተጫራቾች የማይመለስ 575.00 (አምስት መቶ ሰባ አምስት ብር) ከተጨማሪ እሴት ተከስ ጋር በመክፈል የጨረታ ሰነዱን አዲስ አበባ በቅሎ ቤት ጋራጅ ህንጻ 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 432-3-8 ከሚገኘው የግዥ መምሪያ ቢሮ መግዛት ይችላሉ፡፡ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 2,000,000.00 (ሁለት ሚሊዮን ብር) በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ ስም የተዘጋጀ በባንክ በተረጋገጠ ቺክ (C.PO) ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ባንክ ጋራንቲ ከቴክኒክ ዶክመንቶቹ ጋር በማያያዝ ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ መጋቢት 01 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ድረስ በግዥ መምሪያ ቢሮ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡ ጨረታው በእለቱ መጋቢት 01 ቀን 2018 ዓ.ም. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በግዥ መምሪያ ቢሮ ይከፈታል።
ፋብሪካው ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ስልክ 0114420216
ፋስክ 0114420688
አዲስ አበባ
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን
ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ