የባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍ/ቤት ቤት መሸጥ ይፈልጋል


Be’kur(Feb 02, 2026)

የሐራጅ ጨረታ ማስታወቂያ

በአፈ/ከሳሽ አትርሳው አለሙ እና በአፈ/ተከሳሽ እነ ማረው ተሾመ (5) ሰዎች 1ኛ. ማረው ተሾመ፣ 2ኛ.አቶ አስማረ ከበደ፣ 3ኛ.አቶ ደሳለኝ ከበደ፣ 4ኛ.ወ/ሮ ገነት ከበደ፣ 5ኛ. አቶ ሹመት ከበደ መካከል ስላለው የአፈፃፀም ክስ ክርክር ጉዳይ የፈንታ ከበደ ወራሾችን ድርሻ ፤በምስራቅ መንገድ፣ በምዕራብ ባዶ ቦታ፣ በሰሜን ትብለጥ ሁኔ እንዲሁም በደቡብ አትርሳው አለሙ መካከል ተዋስኖ የሚገኘው ቤት በመነሻ ዋጋ ብር 800‚000 (ስምንት መቶ ሽህ ) ይሸጣል፡፡ በመሆኑም የካቲት 14/2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 6፡00 ድረስ በግልጽ ጨረታ ስለሚሸጥ መጫረት የምትፈልጉ ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ በሰአቱና በቦታው በመገኘት ተመዝግባችሁ መጫረት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን፤ የመጨረሻው አሸናፊ ያሸነፈበትን 1⁄4 ኛውን በሞዴል 85 ማስያዝ የሚጠበቅበት መሆኑን እንዲያውቁት ፍ/ቤቱ አዝዟል፡፡

የባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍ/ቤት


Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *