Your cart is currently empty!
የኮልፌ ቀራኒዮ ቁጥር 2 የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤቶች ኃ/የተ/የህ/ስራ ማህበር የነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት በ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት የህንፃ/አጠቃላይ ሥራ ተቋራጮችን በግልጽ በጨረታ የግዢ ዘዴ በመጋበዝ አወዳድሮ ዝቅተኛ ዋጋ ከሰጠው አሸናፊ ከሆነው ሥራ ተቋራጭ ጋር ውል አስሮ የቤት እድሳት ሥራ ማሰራት ይፈልጋል
Addis Zemen(Feb 06, 2026)
የህንፃ እድሳት ሥራ ጨረታ ማስታወቂያ
የኮልፌ ቀራኒዮ ቁጥር 2 የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤቶች ኃ/የተ/የህ/ስራ ማህበር
የኮልፌ ቀራኒዮ ቁጥር 2 የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤቶች ኃ/የተ/የህ/ስራ ማህበር የነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት በ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟላ የህንፃ/አጠቃላይ ሥራ ተቋራጮችን በግልጽ በጨረታ የግዢ ዘዴ በመጋበዝ አወዳድሮ ዝቅተኛ ዋጋ ከሰጠው አሽናፊ ከሆነው ሥራ ተቃራጭ ጋር ውል አስሮ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የቤት እድሳት ሥራ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
1. የውጭ የግድግዳ ቀለም ቅብ
2. የበረንዳ ግድግዳ እና የበር መስኮት ቀለም ቅብ ሥራ
3. የበረንዳ ደረጃ መወጣጫ ብረት ቀለም ቅብ
4. የኮሚናል ቤቶች ስራ ጨምሮ ሥራን ማሰራት ይፈልጋል::
ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ ለምትፈጉ ተጫራቾች መስፈርት :-
1. የ2018 ዓ.ም የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያደሰ እና የ2018 ዓ.ም የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል
2. ደረጃ 6 እና ከዚያ በላይ ያሉ ህንጻ ወይም አጠቃላይ የግንባታ ተቋራጭ ፍቃድ ያለው ( BC or GC)
3. 2 % የጨረታውን ጠቅላላ ዋጋ የጨረታ ማሰከበሪያ ቦንድ በሲፒኦ በስሙ አሰርቶ በቴክኒክ ፖስታ ውስጥ ማስያዝ በተለይ ፖስታ ከቶ ሲፒዮ ብሎ ጽፎ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
4. የጨረታው ሰነዱን ከማህበሩ ጽ/ቤት ወይራ ኮንደምንየም ቁጥር 2 /ወይራ አካባቢ/ማግኘት ይችላሉ።
5. በማይመለስ 500 ብር ገዝቶ መወዳደር ይችላል።
6. የጨረታው ሰነድ ለተጫራቾች የሚሰራጨው ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት10 ተከታታይ የስራ ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል (ቅዳሜ ግማሽ የስራ ቀን ነው)
7. ተጫራቾች የጨረታው ሰነዱን የገዛበትን ደረሰኝ ኮፒ በቴክኒካል ማስገቢያ ውስጥ መከተት አለበት።
8. ማንኛውም ተጫራች የቴክኒክና የፋይናንስ ዶከመንቶችን ለየብቻው በታሸገ የተለያየ ፖስታ ውስጥ ለዚህ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ጋዜጣው በወጣበት በ10ኛው ቀን ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርበታል።
9. ከተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ውጭ የሚመጣ ተጫራች ተቀባይነት የለውም፡፡
10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዚሁ ቀን ከቀኑ 10፡30 ሰዓት የኮልፌ ቀራኒዮ ቁጥር 2 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ባለቤቶች የህ/የተ/ የህ/ስራ ማህበር የሚከፈት ይሆናል፡፡
11. ማንኛውም ተጫራች የሚሰራውን ስራና የቦታውን ሁኔታ በመምጣት ማየት ይኖርበታል፡፡
12. ህብረት ስራ ማህበሩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
13. የጋራ መኖሪያ ቤቶች ህ/ስ/ማህበር ጽ/ቤት (ወይራ ኮንዶሚኒዬም ቀራንዮ ቁጥር 2
ስልክ ቁጥር፡ 0911 961 626 ፤ 0911 199 761 እና 0910 169 455
አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ
የኮልፌ ቀራኒዮ ቁጥር 2 የጋራ መኖሪያ ቤት ባለቤቶች የሀ/የተ/የህ/ ስራ ማህበር