Your cart is currently empty!
ጎሕ ቤቶች ባንክ አ.ማ. ንብረቶች ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Reporter(Feb 08, 2026)
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
ጎሕ ቤቶች ባንክ አ.ማ. ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዘውንና በሠንጠረዡ የተመለከቱትን ንብረቶች በአዋጅ ቁጥር 97/90 (እንደተሻሻለው) መሠረት ንብረቱ ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
በመሆኑም ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት የጨረታ መነሻ ዋጋውን 1/4 (አንድ አራተኛ) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦ በጎሕቤቶች ባንክ አ.ማ. ስም በማሰራትና ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው ለመሳተፍ ይችላሉ።
- የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ አጠቃለው በመክፈል በጨረታ ያሸነፈውን ንብረት መረከብ ይኖርበታል። በእነዚህ ቀናት ውስጥ ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል፡፡ በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦ ይመለስላቸዋል።
- ተበዳሪው/መያዣ ሰጪው በሐራጁ ቀንና ሰዓት በቦታው መገኘት ይችላሉ። ነገር ግን ባይገኙ ሐራጁ በሌሉበት ይካሄዳል።
- የጨረታው አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውንም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን፣ግብር እና ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ወጪዎች ካሉ ገዢ ይከፍላል።
- ንብረቱን በሥራ ሰዓት ፕሮግራም አሲዞ ለመጎብኘት ወይም ለማየት ይቻላል።
- የጨረታው ቦታ አዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 02 የቀድሞ ጃፓን ኤምባሲ ፊትለፊት በሚገኘው የባንኩ ዋና መ/ቤት 6ኛ ፎቅ ላይ በሚገኝ አዳራሽ ነው።
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 87 27 23 35 ወይም 011 668 7390 በመደወል መጠየቅ ይቻላል።
|
የተበዳሪው ስም |
ከተበዳሪዋ የሚፈለግባት ቀሪ ዕዳ |
የመያዣ ስጪው ስም |
ንብረቱ የሚገኝበት አድራሻ |
የጨረታ መነሻ ዋጋ ብር |
ጨረታው የሚካሄድበት ቀንና ዓ.ም |
የምዝገባ ሰዓት |
የጨረታው ሰዓት |
የንብረቱ ዓይነትና አገልግሎት |
የቦታው ስፋት በካ.ሜ |
የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ቁጥር |
|
ወ/ሮ ጽዮን ፍቅሬ ይርጋ |
እስከ ጥር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ብር 1,607,673.56 |
ተበዳሪዋ |
በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክ/ከ ወረዳ 12 |
11,656,132.00 |
መጋቢት 03 ቀን 2018 ዓ.ም |
3፡30- 4፡00 |
4፡00-4፡30 |
አፓርታማ የመኖሪያ ቤት |
114.9 ካ.ሜ |
ቦሌ/12/85//6/9/254829/266531/01 |
|
አንግላ ቢዝነስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር |
እስከ ጥር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ብር 6,348,836.82 |
ወ/ሮ ደስነት ተክሌ ገብረእግዚ |
በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክ/ከ ወረዳ 9 |
5,709,554.27 |
መጋቢት 03 ቀን 2018 ዓ.ም |
4፡45- 5፡15 |
5፡15-5፡45 |
አፓርታማ የመኖሪያ ቤት |
46.8 ካ.ሜ |
ለ/ኩራ/09/36/3/45167/036/15/00 |
|
አንግላ ቢዝነስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር |
እስከ ጥር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ብር 12,919,785.45 |
ወ/ሮ ደስነት ተክሌ ገብረእግዚ |
በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክ/ከ ወረዳ 9 |
8,719,639.52 |
መጋቢት 03 ቀን 2018 ዓ.ም |
8፡00- 8፡30 |
8፡30-9፡00 |
አፓርታማ የመኖሪያ ቤት |
72.83 ካ.ሜ |
ለ/ኩራ/09/33/3/41897/028/7/00 |