Reporter (Jun 07, 2026)
የቀድሞው ስዊድን ኮምዩኒኬሽን ት/ቤት
የሒሳብ ምርመራ ጨረታ ማስታወቂያ
የቀድሞው ስዊድን ኮምዩኒቲ ት/ቤት ወላጆች በጎ አድራጎት ድርጅት ከሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት በስሩ የሚተዳደረውን ት/ቤት ዓመታዊ ሂሳብ በውጪ ኦዲተር ለማስመርመር ይፈልጋል።
ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ቅድመ ሁኔታዎች በመገንዘብ በውጪ ኦዲተርነት ሙያ የተሰማሩና በዚህ ጨረታ ለመወዳደር የሚሹ ድርጅቶች በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ የጨረታ ሰነድ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
1ኛ. የውጪ ኦዲተር ሆኖ መስራት የሚያስችል ሕጋዊ ፈቃድ፤
2ኛ. የ2018 ዓ.ም የንግድ ፈቃድ የታደሰበት ማስረጃ ፤
3ኛ. የዓመቱን ሂሳብ ለመመርመር የሚጠይቁትን የክፍያ መጠን በግልፅ ፋይናንሻል እና ቴክኒካል ፕሮፖዛል ለይቶ ማቅረብ፤
4ኛ. በተለያዩ ድርጅቶች የሰሩባቸውን የሥራ ልምድ ማስረጃዎችና ይህ የሥራ ልምድ መኖሩን የሚመሰክሩ ድርጅቶች ሙሉ አድራሻ ጨምሮ ማቅረብ
አመልካቾች ከላይ የተገለፁትን መረጃዎች በማካተት ይህ ማስታወቂያ በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ ለተከታታይ አስር (10) የሥራ ቀናት በሚከተለው አድራሻ ማቅረብ ይችላሉ።
የቀድሞው ስዊድን ኮምዩኒቲ ት/ቤት ወላጆች በጎ አድራጎት ድርጅት ካሳንቺስ መለስ ፋውንዴሽን ፊት ለፊት አዲስ አበባ
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር +251 91 061 8783/ 251 99 204 8944/+251 91 152 7389 መጠየቅ ይችላሉ።