Addis Zemen (Jun 07, 2026)
የኦዲት ሥራ ጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ አማካሪ መሐንዲሶችና አርክቴክቶች ማኅበር በመዝገብ ቁጥር 1447 በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን የተመዘገበና ፈቃድ ያገኘ የሞያ ማኅበር ነው፡፡ ማኅበሩ የ 2018 የበጀት ዓመት ሒሳብ ለማስመርመር ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ የኦዲት ድርጅቶች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- የንግድ ፈቃድ ያላችሁ፤
- የሙያ ማረጋገጫ ፈቃድ ማቅረብ የምትችሉ፤
- የዘመኑ የመንግስት የሥራ ግብር መክፈላችሁን የምታረጋግጡ፤
- የኦዲት የሥራ ልምድ ያላችሁ፤
- የታክስ መለያ ቁጥር (Tin Number) ያላችሁ መሆን ይኖርባችኋል፡፡
በዚሁ መሠረትም ተወዳዳሪዎች የምታስከፍሉትን ዋጋ እና ሥራውን ሠርታችሁ የምታስረክቡበትን ጊዜ በመጥቀስ የሙያ ደረጃችሁንና ሕጋዊነታችሁን የሚገልፁ ማስረጃዎችን በመያዝ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 (አስር) ተከታታይ ቀኖች ውስጥ ከታች በተቀመጠው አድራሻ እንድታመለክቱተጋብዛችኋል፡፡
አድራሻ ፡–ጉርድ ሾላ፤ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 004
የኢትዮጵያ አማካሪ መሐንዲሶችና አርክቴክቶች ማኅበር