Be'kur (Jun 08, 2026)
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡-0012/2018
የአብክመ ውሀና ኢነርጂ እና የማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ በመደበኛ እና በተለያዩ ፕሮግራም በጀት የቢሮው የተሽከርካሪዎች እና አሽከርካሪዎች ኢንሹራንስ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለአንድ አመት ውል መያዝ ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- ተጫራቾች በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ያላቸው፡፡
- የግዥው መጠን በየንግድ ዘርፉ 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ብር በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን
የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡ - ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-2 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የኢንሹራንሱ ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፍኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) 30,000 (ሰላሳ ሽህ) ብር በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ
ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው፡፡ - በጨረታው ፍላጎት ያላቸው ህጋዊ ድርጅቶች ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የአብክመ ውሀና ኢነርጂ ቢሮ ቁጥር 23 በመቅረብ የማይመለስ የኢትዮጵያ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) ብቻ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት የሚቻል ሲሆን ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዶችን ሲመልሱ የድርጅቱ ህጋዊ ማህተም፣ ፊርማ እና አድራሻ በትክክል በመሙላት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ክፍት ሆኖ በ16ኛው ቀን 8፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከቀኑ 8፡30 ይከፈታል፡፡ ቀኑ የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ስዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ውሀና ኢነርጂ ቢሮ ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ከአሁን በፊት የመንግስት ግዥዎች ላይ ተሳትፈው አሸናፊ መሆናቸው ተገልፆላቸው ቀርበው ውል ለመያዝ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ወይም ውል ይዘው በአግባቡ ባለመፈፀማቸው እርምጃ ያልተወሰደባቸው መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ ሆኖም የተወሰደው እርምጃ በማስረጃ የተደገፈ መሆን አለበት፡፡
- ውል ከተያዘበት ቀን ጀምሮ ያለምንም የዋጋ ለውጥ ለአንድ ዓመት የጸና መሆን ይኖርበታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በአካል ወይም በስልክ ቁጥር 058 222 01 32/058 220 1087 ዘወትር በስራ ቀናት መጠየቅ ይችላሉ፡፡
- አድራሻ የአብክመ ውሀና ኢነርጂ ቢሮ ቀበሌ 07 ባህር ዳር ዩንቨርስቲ ዊዝደም ፊት ለፊት ይገኛል፡፡
የአብክመ ውሀና ኢነርጂ እና የማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ