Addis Zemen (Jun 09, 2026)
የ6ኛ ዙር የመኖሪያ/ገስት ሀውስ ቤቶች ኪራይ
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቀጥር ፌ.ቤ.ኮ/ብ.ግ.ጨ/አገ/12/09/2018
1. የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በሥሩ የሚገኙ ውስጥ ለመኖሪያ/ ገስት ሀውስ አገልግሎት የሚውሉ ቤቶችን በጨረታ መለያ ቁጥር ፌ.ቤ.ኮ/ብ.ግ.ጨ/አገ/12/09/2018 ተጫራቾችን አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል።
2 ኮርፖሬሽኑ ለሚያከናውነው የመኖሪያ/ ገስት ሀውስ ቤቶች ኪራይ ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውንና የመወዳደሪያ ተመን ዋጋ በአንድ ፖስታ ማቅረብ አለባቸው።
3. ጨረታው የሚከናወነው በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ሥነ–ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትና ይኸንኑ አስመልክቶ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን መመሪያ መሠረት ነው።
4. ማንኛውም ፍላጎት ያለው ተጫራች የተሟላ የጨረታ ሰነዱን ከሰኔ 01 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ቅዳሜን ጨምር ባሉት 21 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ከ2፡00 እስከ 11፡00 ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 6፡00 ድረስ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በካሽ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድን ለገሐር በሚገኘው በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት በአካል በመቅረብ መግዛት ይችላሉ::
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዶቻቸውን በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት በሚገኘው ዋና የመሰብሰቢ አደራሽ 1ኛ ፎቅ ለዚሁ ታሽጎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው በመጀመሪያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21ኛው ቀን ወይም ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሰዓት 11፡00 ሰዓት ድረስ እንዲያቀርቡ ሆኖ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 25,000.00 /ሃያ አምስት ሺሕ ብር/ በሁኔታዎች ላይ ያልተመሠረተ ሲ.ፒ.ኦ በፌደራል ቤቶች ኮፖሬሽን ስም ከጨረታ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው። ከጨረታው መክፈቻ ዕለትና ጨረታው ሰዓት ዘግይቶ የቀረበ የጨረታ ሰነድ ውድቅ ይደረጋል፤ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጨረታ ሰነዱ ክፍል 1 ላይ በተገለጸበት ቀንና ሰዓት ይከፈታል።
6. ተጫራቾች ቤቶቹን በአካል ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ማብቂያው ቀን ድረስ በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 3:00 እስከ ቀኑ 11፡00 ሰዓት ቤቶቹ በሚገኙበት አድራሻ ድረስ በመቅረብና ለዚሁ ሥራ በሚመደቡ ባለሙያዎችና በሚወጣው ፕሮግራም መሠረት ቤቶቹን መመልከት ይችላሉ።
7 ኮርፖሬሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ለተጨማሪ መረጃ
በስልክ ቁጥር 0910-48-59-48 0922-49-18-85 ወይም 0922-98-7633 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል::
ዌብሳይት/ website www.fhc.gov.et
የፖ.ሣ.ቁ. PO Box 299
ፋክስ ቁጥር፡ 011-5-54-60-45 / 011-5-52-46-46
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን