Addis Zemen (Jun 06, 2026)
ድጋሜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ መለያ ቁጥር ግ/ጎማ/02/2018
የሀዋሳ ከተማ መ/ው/ፍ/አዝ/ድርጅት የመኪና ጎማ ከነከመነዳሪ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል።
ስለዚህ በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልግ ድርጅት ከዚህ በታች በሰንጠረዥ በተገለፀው ዝርዝር መሠረት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ ።
|
ሎት |
መግለጫ |
መለኪያ |
ብዛት |
|
1 |
የከባድ መኪና ጎማ ከነመነዳሪ |
በቁጥር |
49 |
|
2 |
የትንሽ(የቀላል) መኪና ጎማ ከነመነዳሪ |
በቁጥር |
50 |
በጨረታው ለመዳደር የሚፈልጉ ድርጅት ከዚህ በላይ በተገለፀው ዝርዝር መሠረት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ።
ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፡–
1. ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የ2018 ዓ/ም የዘመኑን ግብር የተከፈለበት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችል፣ በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለው፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ( የቫት) ተመዝጋቢ የሆነ፣
2. የጨረታ ዋስትና መያዣ ብር 50,000 (ሃምሳ ሺህ ብር ብቻ) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ግዥውን በሚፈፅመው ድርጅት ስም ተዘጋጅቶ ማቅረብ ይኖርበታል። ከተጠየቀው ዉጪ የሚቀርብ ማስረጃ ተቀባይነት የለውም።
3. የተዘጋጀውን (ዕቃ)የመኪና ጎማ ከነከመነዳሪ መጠንና ዓይነት ዝርዝር መረጃ የሚገልፅ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00/አምስት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ከሀዋሳ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የግዥ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 19 ቀርበው መግዛት ይችላሉ።
4. ተጫራቾች አንድ ተጫራች በሰጠው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስተት የተከለከለ ነው።
5. ተጫራቾች በሰነዶቻቸው ላይ ስማቸውን ሙሉ አድራሻቸውን ፊርማቸውን አሟልተው ማቅረብ አለባቸው::
6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ዋናውን እና 2 (ሁለት) ኮፒ ለየብቻ በማድረግ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ ሰነዶችን ማቅረብ አለባቸው።
7. ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ16 ተከታታይ ቀናት ከጠዋት 2፡30 ሰዓት እስከ 11፡00 ሰዓት ድረስ ከሀዋሳ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ግዥ አስተዳደር ቡድን መሪ ቢሮ ቁጥር 19 በመምጣት የተዘጋጀውን የጨረታ ዶክመንት መግዛት ይችላሉ።
8. ጨረታው የሚከፈተው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ17ኛው ቀን ላይ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 8፡00 ሰዓት ድረስ ድርጅቱ ለጨረታ ባዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው። ጨረታው በዕለቱ በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሀዋሳ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል። ሆኖም 17ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
9. ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር፡– 046 212 1580 / 046 212 9112
አድራሻ፡– ከወልደአማኑኤል አደባባይ በግራ በኩል ወደ አዲሱ መናኸሪያ በሚወስደው መንገድ 200 ሜትር አስፋልት ፊት ለፊት
የሀዋሳ ከተማ መጠጥ ውሃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት