Addis Zemen (Jun 06, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የወላይታ ሶዶ ከተማ አስ/ር ከፍተኛ ፍ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ከካፒታል በጀት ተሽከሪካሪ ወንበር፣ LCD projector እና ላፕቶፕ ኮምፒውተር በግልጽ ጨረታ መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልግ ተጫራች፡–
1. በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው
2. የተጨማሪ እሰት ታክስ /ቫት/ ተመዝጋቢ የሆኑበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፤
3. ዝርዝር የጨረታ ሠነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የወላይታ ሶዶ ከተማ አስ/ር ከፍተኛ ፍ/ቤት ግዥ ክፍያ ንብረት አስ/ር ደጋፍ የሥራ ሂደት በመቅረብ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል መግዛት ይኖርባቸዋል።
4. ተጫራቾች ብር 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ብቻ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ /CPO/ ከጨረታው ሠነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
5. ተጫራቾች የሚያቀርቧቸውን የዋጋ ማቅረቢያ ሠነዶቻቸውን ኦርጅናሉን በታሸገ ፖስታ ሙሉ አድራሻቸውን በመጥቀስ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት እስከመጨረሻው ቀን ከቀኑ 11፡30 ሰዓት ድረስ ለዚህ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ የጨረታ ሠነዱን ማስገባት አለባቸው።
6. በጨረታው ሠነድ የተፃፈውን ዕቃ ዓይነትና መለያ ቁጥሩን ተጫራቾች በትክክል መሙላት አለባቸው። የሚያቀርቧቸው ዋጋ ከቫት ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ15ኛው ቀን ከቀኑ 11፡30 ታሽጎ በሚቀጥለዉ ቀን ማለትም በ16ኛው ቀን 4፡30 ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 16ኛው ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው ሥራ ይከፈታል።
8. ያሸነፈ ተጫራች ዕቃውን እስከ መ/ቤቱ ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። አሸናፊ ተጫራች የዕቃዉ ናሙና ማቅረብ አለባቸው።
ፍርድ ቤቱ ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን መለወጥ ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የወላይታ ሶዶ ከተማ አስ/ር ከፍተኛ ፍ/ቤት