Be'kur (Sep 07, 2026)
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በታች አርማጭሆ ወረዳ የሳንጃ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በ2019 ዓ.ም ለመ/ቤቱ አገልግሎት የሚውል 1hz-k79 አንቡላንስ መኪና መለዋወጫ እቃ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ።
- በዘመኑ ታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው።
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው።
- አሽናፊዉ ተለይቶ ዉል ከወሰደበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2019 ዓ.ም ተቋሙ ሲፈልግ ለማቅረብ ዉል መዉሰድ የሚችል።
- የግዥው መጠን ከብር 100,000 (አንድ መቶ ሽህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-5 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከማጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- የሚገዙ የመለዋወጫ እቃ አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል የሳንጃ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግ/ፋ/ን/አስ/ቢሮ መውሰድ ይችላሉ። ጨረታው ከወጣበት ከጳጉሜ 02/2018 ዓ/ም እስከ መስከረም 11/2019 ዓ/ም ለተከታታይ 15 ቀናት ይቆያል።
- የጨረታው ሳጥን የሚታሸገው መስከረም 12/2019 ከረፋዱ 3፡30 ይሆናል።
- ጨረታው የሚከፈተው ሁሉም ተጫራቾች ወይም ወኪሎች በተገኙበት በሳንጃ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አዳራሽ መስከረም 12/2019 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ይሆናል። ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸዉ ባይኖርም የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት አንድ በመቶ የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው።
- ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በሁለት ፖስታ ኦርጀናልና ኮፒውን በተለያየ ለየብቻ በመለየት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- አሸናፊው ድርጀት በዓ/ህግ ጽ/ቤት ቀርቦ ውል መውሰድ የሚችል።
- ከጨረታ ሰነዱ ላይ ከተቀመጠው የዋጋ መሙያ ፎርም በስተቀር በማሳሰቢያ የሚሞሉ የዋጋና ሌሎች አላስፈላጊ መረጃዎችን የማንቀበል መሆኑን እንገልፃለን።
- አሸናፊ ድርጅት የውል ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን 10 በመቶ ማስያዝ የሚችል።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ብሄራዊ በዓል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል።
- የሚያቀርቡት የመኪና መለዋወጫ እቃ ሁሉም እቃዎች ኦርጀናል መሆን አለባቸው። ኦርጂናል ለመሆኑ በባለሙያ (በሹፌር) እየተረጋገጠ ወደ ንብረት ክፍል ገቢ ይደረጋል። በመሆኑም እንዲያቀርቡ የተጠየቀዉን እቃ በአንድ ቀን ዉስጥ ማቅረብ የሚችል።
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 18 19 85 88 /09 34 62 32 87 ደውለው መረጃ መጠየቅ ይችላሉ።
የሳንጃ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል