Your cart is currently empty!
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገ/ጽ/ቤት ግ/ፋ/ን/አስ ቡድን የተለያዩ የጽህፈት መሳሪያዎች እና የተለያዩ የጽዳት እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል
Addis Zemen(Oct 17, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታው አይነት መደበኛ፣ ጨረታ ቁጥር፡– 1/2018
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገ/ጽ/ቤት ግ/ፋ/ን/አስ ቡድን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል።
1. የተለያዩ የጽህፈት መሳሪያዎች፣
2. የተለያዩ የጽዳት እቃዎች፣
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች እንዲወዳደሩ ይጋብዛል።
1. በዘመኑ የታደሰ የህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው፣
3. የግዥ መጠን ብር 200,000.00/ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ወይም /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
5. የጨረታ ስፔስፊኬሽን /ዝርዝር መግለጫ/ ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይቻላሉ።
6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን መግዥያ ለጽህፈት መሳሪያዎች የማይመለስ 100/ አንድ መቶ ብር/ እና እንዲሁም ለጽዳት እቃዎች የማይመለስ 50/ሃምሳ ብር/ በመክፈል ከግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን ድረስ ሰነድ በመግዛትና ዋጋ በመሙላት ማስገባት ይችላሉ።
7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለጽህፈት መሳሪያ 20,000/ ሃያ ሺህ ብር/፣ ለጽዳት እቃዎች 5,000 / አምስት ሺህ ብር/ በሲፒኦ ከህጋዊ ባንክ ወይም በመሂ 1 ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው። ልዩ ልዩ መረጃዎች ፎቶ ኮፒ አድርገው ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዝ ይጠበቅባቸዋል።
8. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በማሸግ በገ/ጽ/ቤት በግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን በግዥ ቢሮ ቁጥር 39 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን ከቀኑ 7፡45 ሰዓት ድረስ ሰነዱን ዋጋ ሞልተው ማስገባት ይኖርባቸዋል።
9. ጨረታው የሚከፈተው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ወይም ባይገኙም በግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ግዥ ቢሮ ቁጥር 39 የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተቆጥሮ በ16ኛው ቀን ከቀኑ 7፡45 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን 8፡00 ሰዓት ላይ ይከፈታል፣ ነገር ግን የስራ ቀን ካልሆነ ግን በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ስዓት ታሽጎ በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
10. ከላይ የተጠቀሰው ጨረታ አሸናፊው የሚለየው ለመ/ቤቱ በሚያስገኘው ጥቅም ይሆናል።
11. የጨረታው አሸናፊ ለሆነው ተወዳዳሪ እቃዎቹን አቅርቦ ክፍያ ሲፈጸምለት ከ20,000/ ሃያ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ 3% ዊዝ ሆልዲንግ ወይም የቅድመ ግብር ክፍያ የሚቀነስበት መሆኑን መታወቅ አለበት።
12. የጨረታ ጊዜ/ስዓት ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ምንም አይነት ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይቻሉም፡፡
13. የቀረበው የዋጋ መወዳደሪያ ጨረታው ከተከፈተበት ዕለት አንስቶ ለ30 ቀናት ጸንቶ ይቆያል።
14. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
15 ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከጨረታ ሰነዱ እና ከተጫራቾች መመሪያ ላይ ያገኛሉ እንደዚሁም ቢሮ ቁጥር 39 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 011-685-1529/28 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።
የመ/ሜዳ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ፋ/ን/አስ ቡድን