Your cart is currently empty!
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መሬት አስተዳደር እና ኢንቨስትመንት ቢሮ የመስክ ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል
Addis Zemen(Oct 27, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 001/2018
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መሬት አስተዳደር እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ከዚህ በታች የተገለጹትን የመስክ ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል።
|
No |
Item |
Quantity |
|
1 |
መ/ቤታችን የሚከራይ የመስክ ተሽከርካሪዎችን ከ10-12 መቀመጫዎች ያሉትን ለመከራየት ይፈልጋል ፡፡ |
3 |
በዚህ መሰረት፡–
1. በመሰኩ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፤
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው ፤
3. የቫት ተመዝጋቢነት ሰርተፍኬት ያላቸው ፤
4. ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነት ያላቸው ::
5. የዕቃና አገልግሎት አቅራቢነት ሰርተፍኬት ያላቸው ፤
6. የዘመኑን ግብር ስለመክፈላቸው ከሚመለከተው አካል የተሰጣቸው የግብር ከፋይነት ሰርተፍኬት ያላቸው።
7. የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መሬት አስተዳደር እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሁለተኛ ፎቅ ቁጥር 11 ለእያንዳንዱ ተሽከርካሪ የማይመለስ 100 (አንድ መቶ) ብር በመክፈል መግዛት ይችላሉ።
8. ጨረታው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 የሥራ ቀናት አየር ላይ ይውላል።
9. ተጫራቾች የጨረታ መወዳደሪያ ሀሳባቸውን ጋዜጣው ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10ኛው ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ድረስ ቢሮ ቁጥር 11 ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው። ጨረታው አየር ላይ መቆያው ጊዜ ባበቃበት ቀን 6፡00 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ጨረታው በጋዜጣ የሚውልበት የመጨረሻ ቀን በዓል፣ ቅዳሜ ወይም እሁድ የሚውል ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል።
10. ተጫራቾች 50,000 (ሀምሳ ሺህ) ብር የጨረታ ማስከበሪያ በ CPO ማስያዝ አለባቸው ቢሮ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሠረዝ መብት የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 15 69 25 35 / 09 16 35 78 76 ደውሎ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን።
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መሬት አስተዳደር እና ኢንቨስትመንት ቢሮ