Your cart is currently empty!
ሕብረት ባንክ ከረቫትና የጥበቃ ካፖርት በጨረታ ለመግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Feb 08, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ሕባ/021/18
ሕብረት ባንክ ከዚህ በታች የተገለፁትን ከረቫትና የጥበቃ ካፖርት በጨረታ ለመግዛት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
ዝርዝር መግለጫ |
መለኪያ |
ብዛት |
ምርመራ |
|
1 |
ከረቫት (ለወንድ) |
በቁጥር |
840 |
|
|
2 |
ከረቫት (ለሴት) |
በቁጥር |
108 |
|
|
3 |
ካፖርት |
በቁጥር |
79 |
|
ስለሆነም ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው ተጫራቾች ከዚህ በታች በተገለፀው መሠረት የጨረታ ሰነዱን ገዝተው መወዳደር ይችላሉ።
- ተጫራቾች ለዚህ ጨረታ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ) በአካውንት ቁጥር IN0403007 አቅራቢያቸው በሚገኝ በማንኛውም የሕብረት ባንክ ቅርንጫፍ ገቢ በማድረግ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- የጨረታ ሰነዱን ሰንጋ ተራ በሚገኘው የባንኩ ዋና መ/ቤት ሕንፃ 19ኛ ፎቅ ግዥ ዋና ክፍል በመገኘት መግዛት ይቻላሉ።
- ተጫራቾች በጨረታ መመሪያው መሠረት የጨረታ ሰነዱን ሞልተው ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- በጨረታ ሰነዱ ላይ የተገለፀውን መመሪያ ያልተከተለ ተጫራች ከውድድር ሊታገድ ይችላል።
- እያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ በታሸገ ኤንቨሎፕ መቅረብ አለበት።
- እያንዳንዱ ተጫራች በጨረታ ሰነዱ ላይ የተገለፀውን የጨረታ ማስከበሪያ (ቢድ ቦንድ) ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ወይም በታሸገ ኤንቨሎፕ ውስጥ በማድረግ ማቅረብ ይኖርበታል።
- ተጫራቾች የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ባንኩ ዋና መስሪያ ቤት 19ኛ ፎቅ ማስገባት ይችላሉ።
- ጨረታው የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ባንኩ ዋና መስሪያ ቤት 4ኛ ፎቅ ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ከህብረት ባንክ ውጭ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011 467 3208 ወይም 011 470 6541 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
ሕብረት ባንክ