Addis Zemen (Apr 08, 2026)
በድጋሚ የወጣ ግልጽ ጨረታ
ማስታወቂያ ቁጥር 03/2018
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የደሀና ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለደ/ወ/ግብርና ፅ/ቤት በEU ፕሮጀክት በጀት 019 ቀበሌ አመላ ለሚገነባው መስኖ ፕሮጀክት አገልግሎት የሚውል ፤
- የኮንስትራክሽን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች፤ የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ በመሆኑ ይጋብዛል።
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፤
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር(1) ነበር ያላቸው
- የግዥ መጠን ጥቅል ዋጋ ከ200,000 (ሁለት መቶ ሺህ)ብር በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር እያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ ቫትን ጨምሮ 150,000/አንድ መቶ አምሳ ሺህ ብር ብቻ፣ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒዩ ወይም በጥሬገንዘብ ከመ/ቤታችን ገ/ያዥ ገቢ በማድረግና ገቢ ያደረገበትን ደረሰኝ ኮፒ በማድረግ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
- የእቃውን አይነት ዝርዝር መግለጫ/ስፔስፊኬሽን /ከጨረታ ሰነድ ማግኝት ይችላሉ፤
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 250/ሁለት መቶ ሃምሳ ብር ብቻ/ በመክፈል ጨረታዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት መግዛት ይችላሉ።
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጆች ማለትም ዋና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸኝ ፖስታ ደ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 1 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ይህ ጨረታ በጋዜጣ በወጣበት በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 (አራት ሰዓት) ላይ ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡30 ይከፈታል።
- ጨረታው በሚከፈትበት ቀን ካላንደር ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ስዓት ይከፈታል
- መ/ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
- ጨረታው ስርዝ ድልዝ ወይም የማይነበብ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
- በዚህ የጨረታ ማስታወቂያ ያልተካተቱ ህግና ደንቦች በግዥ መመሪያ ቁጥር1/ 2003 ተግባራዊ ይደረጋል።
- አቅርቦቱ 09 ቀበሌ አመላ መስኖ ፕሮጀክት ከሚገነባው የመስኖ ግንባታ ድረስ መሆኑ ይታወቅ ተጫራቾች፤ይህ መስኖ ፕሮጀክት ትልልቅ መኪናዎቹን የሚያስገባ መሆኑ መገንዘብ ይኖርባቸዋል
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ሁሉ የጨረታውን ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በወረዳው ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 8 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ 033 461 0335 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።
በአብክመ በበዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የደሀና ወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብ/ጽ/ቤት