Addis Zemen (Apr 11, 2026)
የጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን የምዕራብ ዓባያ ወረዳ ፋይናንስና ፕላን ልማት/ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል ሞንታርቦ ድጂታል ፎቶ ካሜራ እና ሌሎች የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚሁ መሠረት፡-
1. በዘርፉ የንግድ ፍቃድ ያለውና የዘመኑን ግብር የከፈለ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር) ያለው፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገበ፣ የአቅራቢዎች ዝርዝር ወይም በመንግስት ኤልክትሮኒክ ግዥ ሥርዓት (E-GP system) የተመዘገበ፣
2. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 30,000 (ሠላሳ ሺህ) በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
3. ተጫራቾች ጨረታዉ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት በወረዳው ገቢዎች ባለሥልጣን ቅ/ጽ/ቤት በመቅረብ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ) በመክፈል እና ደረሰኙን በመያዝ የጨረታውን ዝርዝር የያዘውን ሰነድ ከም/ዓ/ወ/ ፋ/ጽ/ቤት መውሰድ ይችላሉ፡፡
4.ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በማሸግ ሙሉ አድራሻውን በመግለጽ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን እንዲጨምሩ እያሳሰብን ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ በወጣ በ16ኛው የሥራ ቀን በጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ይታሸጋል፡፡
5. ጨረታው በ16ኛው የሥራ ቀን ልክ 4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ ሥራ ቀን ላይ በተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
7. የጨረታው ሣጥን ምዕራብ ዓባያ ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 11 ይገኛል፡፡
8. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብት የተጠበቀ ነው። ምስ በለ
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 0464520015/0464520009
በጋሞ ዞን ምዕራብ ዓባያ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት
(ብርብር)