Addis Zemen (Apr 25, 2026)
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በኮ/ቀ/ክ/ከ/ቀ/ጤ/ጣ/ በ2018 በጀት ዓመት የሁለተኛ ዙር ግልፅ ጨረታ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚህ መሠረት፤
- ሎት 1. የጠቅላላ ጥገና
- ሎት2. የፅኅፈት መሳሪያዎች
በዕቃ አቅራቢነት የተመዘገበና የታደሰ ንግድ ፍቃድና ተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ እና የጨረታ ማስከበሪያ ከታወቀ ባንከ ሲፒኦ ሎት1፤ 9,000 ሎት2 10,000.00 ማስያዝ የሚችል።
- የጨረታው አሸናፊ ድረጅት የውል ማስከበሪያ 10% ሲፒኦ ማስያዝ የሚችል።
- የጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጃችሁ በሙሉ መወዳደር የምትችሉት ባመረታችሁት ዕቃ ብቻ ሲሆን አምራች መሆናችሁን የሚገልፅ ደብዳቤ በአደራጃችሁ ፅ/ቤት ኃላፊ የተፈረመ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዛችሁ ማቅረብ ይኖርባችኋል።
- አንዱ በሰጠው ዋጋ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት አይቻልም።
- ተጫራቾች ሰነድ ለማስገባት ሲመጡ ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን ለየብቻ በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት አለባቸው።
- የጨረታ ሰነዱን መሸጫ በየሎቱ ዋጋ ብር 300.00 ነው።
- ከዚህ በላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት የሚችል ተጫራች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በተቋሙ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 59 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለበት። ጨረታው በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ማሳሰቢያ ፤
- ጤና ጣቢያው በጨረታው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ጤና ጣቢያው ለጨረታ አሸናፊው ውል ከመዋዋሉ በፊት 20% ወደላይ መጨመር 20% ወደታች መቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተወዳዳሪዎች ለአሸነፉት ዕቃ ባስገቡት ናሙና መሠረት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- የሚቀርቡትን ዕቃዎች በተቋሙ ጥራት ኮሚቴ ማሳየት ይጠበቅባቸዋል።
አድራሻ ፤
ከጦር ኃይሎች ወደቀራንዮ የሺደበሌ በሚወስደው መንገድ ወረዳ 08 ፅ/ቤት በስተጀርባ ቀ/ጤ/ጣቢያ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፤ 011 383 9040
በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቀራንዮ ጤና ጣቢያ