Addis Zemen (May 09, 2026)
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የወለይታ ዞን ፋይናስ መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት ለወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ከዚህ በታች በሎት የተጠቀሱ ዕቃዎች ግዥ በዘርፉ ከተሰማሩ አቅራቢዎች ለመፈጸም ይፈልጋል፡፡
|
ሎት |
የግዥ አይነት |
የጨረታ ማስከበሪያ |
|
ሎት 1 |
የሶላር ሙዘራት ግዥ |
60,000 |
|
ሎት 2 |
የውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር ግዥ |
60,000 |
ስለዚህ ተጫራቾች፡–
1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ስራ ፈቃድ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ሰርተፍኬት፣ የታክስ ከፋይነት ማረጋገጫ (ቲን) ሰርተፍኬት እና የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው፡፡
2. ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ የያዘ ሰነድ ለመግዛት ሲመጣ የንግድ ፈቃድ ኮፒ ብር 100/ አንድ መቶ/ እየከፈሉ ከወላይታ ዞን ፋይናንስና ፕላን መምሪያ 2ኛ ፎቅ ከቢሮ ቁጥር 3 ይህ ማስታውቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ።
3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በመ/ቤቱ የገቢ ደረሰኝ በጥሬ ገንዘብ በማስያዝ ከኦሪጅናል የጨረታ ሀሳብ ጋር አሽገው ማቅረብ አለባቸው።
4. ተጫራቾች የአንዱን ዕቃ ወይም አገልግሎት ዋጋ የሚያቀርቡበትን የመወዳደሪያ ሀሳባቸውን በጨረታ ሰነድ ላይ በተዘጋጀው ዋጋ መሙያ በመሙላት በታሸገ ፖስታ በወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን በጨረታ አድራሻ ቢሮ ቁጥር 19 መክተት ይኖርባቸዋል፡
5. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያውን ሰነድ አንድ ኦሪጅናል እና 1 የኦርጅናሉን ፎቶ ኮፒ ለብቻ በሰም በታሸገ ሳጥን ውስጥ መከተት ይኖርባቸዋል፡፡ ኤንቨሎኘ ሙሉ አድራሻቸውን በመጥቀስ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ መክተት ይኖርባቸዋል፡፡
6. ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር ለ15 ተከታታይ ቀናት አየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን በ8፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በዕለቱ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመምሪያው የጨረታ አዳራሽ ይከፈታል። 16ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
7. አሸናፊ ድርጅት አስፈላጊውን ውለታ በመፈጸም ዕቃውን እገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ ወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ድረስ በማቅረብ ገቢ ሲያደርግ ሲጨርስ ክፍያ የሚፈጸም ይሆናል፡፡
8. ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 046 551 2116 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የወላይታ ዞን ፋይናንስና ፕላን መምሪያ