Your cart is currently empty!
በደ/ምዕ/ኢት/ህ/ክ/መንግስት የኮንታ ዞን በ2018 በጀት ዓመት ለሴ/መ/ቤቶች የተለያዩ መኪና ጥገና እና ለእሞታ አዳሪ ት/ቤት የተለያዩ ፈርኒቸሮችን በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Aug 19, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በደ/ምዕ/ኢት/ህ/ክ/መንግስት የኮንታ ዞን በ2018 በጀት ዓመት በሎት1 ለሴ/መ/ቤቶች የተለያዩ መኪና ጥገና እና በሎት2 ለእሞታ አዳሪ ት/ቤት የተለያዩ ፈርኒቸሮችን በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚሁ መሠረት ለመጫረት የምትፈልጉ፡–
1/ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣
2/ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፤
3/ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) ፤
4/ በመንግስት ግዥ ላይ የአቅራቢነት ሰርተፊኬት፤
5/ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስከር ወረቀት፣ እና
6/ መልካም ሥራ አፈፃፀም በየዘርፉ የ2016 ወይም 2017 ዓ.ም ኮፒ ማቅረብ የሚችል፤ በ2018 በጀት ዓመት ፈቃድ ያወጡትን የመልካም ሥራ አፈፃፀም አይመለከትም።
7/ ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ሎት የጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ ብር 50,000 (ሃምሳ ሺህ) ብር የጨረታ ማስከበሪያ ከታወቀ ባንከ በCPO ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
8/ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ 21ኛው ቀን ድረስ በኮንታ ዞን ፋ/መምሪያ የጨረታ ዶክመንት በመግዛት እና በዋጋ ማቅረቢያ በመሙላት ቴከኒካል አንድ ፋይናንሻል ኦሪጅናል 1 እና ፋይናንሻል ኮፒ 2 በድምሩ 4 ፖስታ የድርጅታችሁን ማህተም በማድረግ በጨረታ ፖስታ በማሸግ በኮንታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለዚሁ ዓላማ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
9/ በተራ ቁጥር 8 መሠረት የጨረታ ሣጥን የሚከፈተው ከላይ በተባለው በ22ኛው ቀን ሲሆን ይህ ቀን የመንግሥት ሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ታሸጎ በዚሁ ዕለት በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኮንታ ዞን ፋ/መምሪያ ይከፈታል።
10/ ተጫራቾች የጨረታ ዶክመንት የማይመለስ 200 (ሁለት መቶ ብር) በመከፈል ከኮንታ ዞን ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 9 ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
11/ ተጫራቾች ጨረታውን አሸንፈው ውል በመግባት ንብረቱን አስከ ኮንታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ እመያ ከተማ ድረስ ማቅረብ አለባቸው።
12. በዚህ የጨረታ ማስታወቂያ ላይ የተገለፁትን መስፈርቶችን የማያሟላ ተጫራች ለቴክኒካል ግምገማ አይቀርብም።
13/ መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡– 0917 388 691 / 0917 161 785 ወይም 0910 262 925
አድራሻችን፡– በደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መንግስት ኮንታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ከጅማ ከተማ በስተ ደቡብ 102 ኪ.ሜ በአመያ ከተማ ይገኛል።
በደ/ም/ኢ/ህ/ክ/መንግስት የኮንታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ