በጅማ ዞን በዴዶ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት በ2018 የበጀት ዓመት የተለያዩ እቃዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen(Aug 22, 2025)

Please read the detailed instructions below. ከስር የተቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።

የጨረታ ማስታወቂያ

በጅማ ዞን በዴዶ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት በ2018 የበጀት ዓመት የተለያዩ

  • የሥራ ግብይቶችን፣ የጽህፈት እና ንጽህና መጠበቂያ መሳሪያዎችን፣
  • የግንባታ እቃዎችን፣ የፈርኒቸር እና የቢሮ ቋሚ እቃዎችን፣ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን፣
  • አጠቃላይ የመኪና ጥገና ጋራዦችን እና የመኪና እቃ መለዋወጫ /spare- part/፣
  • የተለያዩ የመኪና ጎማዎችን፣ የተለያዩ የሞተር ሳይክሎችን፣
  • የተለያዩ ጨርቃጨርቆችን እና የጤና ባለሙያ የደንብ ልብሶችን፣ የሆስፒታል እና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እቃዎችን ጨምሮ በግልጽ ጨረታ ተጓዳኝ እቃዎችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

የመወዳደሪያ መስፈርቶች፡-

  1. በዘርፉ የዘመኑ የታደሠ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፤
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
  3. ተወዳዳሪዎች በንግድ እና ከተማ ልማት ጽ/ቤት በስነ-ምግባር ጉድለት ያልተከሰሱ መሆኑን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
  4. የግብር መለያ ቁጥር (Tin No) ማቅረብ የሚችሉ፤
  5. የፌዴራልና የፋይናንስ ግዥ ስርዓትን የሚያከብሩ፤
  6. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆኑና ለዚህም ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
  7. የጨረታ ማስከበሪያ ማረጋገጫ የሚሆን 10,000 (አስር ሺህ) ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
  8. ጨረታውን ያሸነፈው አካል የመንግሥት ግዢ አገልግሎት በሚያዘው መሠረት 2% (ሁለት ፐርሰንት) TOT ግብር የመክፈል ግዴታ አለባቸው፡፡
  9. ተወዳዳሪዎች የአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ መመዝገባቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
  10. ተወዳዳሪው በሰነዱ ላይ ትክክለኛ አድራሻ፣ ስምና ፊርማ ማሳረፍ የሚችሉ፡፡
  11. ጨረታው ላይ የሚሳተፉ ተጫራቾች በሙስና እና ወንጀል ነክ መሰል ነገሮች ያልተከሰሱና ነፃ የሆኑ መሆን አለባቸው፡፡
  12. ሁሉም ተወዳዳሪዎች ከጨረታው ሰነድ አንድም ሳያጎሉ ሞልተው መመለስ አለባቸው፡፡
  13. ተወዳዳሪዎች የሚያቀርቡት እቃዎች ጥራት ያለው መሆን አለበት፡፡
  14. የጨረታው ሰነድ ከ16/12/17 ዓ.ም እስከ 5/01/2018 ዓ.ም 11:30 ሰዓት ድረስ በዴዶ ወረዳ ሀገር ውስጥ ገቢዎች ባለስልጣን ቢሮ ቁጥር 7 ቀርባችሁ የማይመለስ የኢትዮጵያ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) ከፍላችሁ የጨረታውን ሰነድ መግዛት ትችላላችሁ፡፡
  15. የጨረታው ሰነድ ሳጥን የሚዘጋው በ6/01/2018 ቀን በ4፡00 ሰዓት ሆኖ የሚከፈትበት በ 6/01/2018 ዓ.ም በ4፡30 ሰዓት በዴዶ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 104 ህጋዊ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ተወካይ ባሉበት ጨረታው ይከፈታል፡፡

መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር፡-09-17-87-89-61/ 09-45-03-41-39
በጅማ ዞን በዴዶ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት