Your cart is currently empty!
በልደታ ክፍለ ከተማ የወ/ሮ በለጥሻቸው የህዝብ ጤና ጣቢያ የተለያዩ እቃዎችን ግዥ አገልግሎት መፈፀም ይፈልጋል
Addis Zemen(Sep 07, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥው መለያ ቁጥር 01/2018
በልደታ ክፍለ ከተማ የወ/ሮ በለጥሻቸው የህዝብ ጤና ጣቢያ የ2018ዓ.ም በጀት ዓመት መግዛት የሚፈልጋቸውን
- ሎት 1፡– የተለያዩ የደንብ ልብስ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 4000.00
- ሎት 2፡– የፅህፈት መሳሪያ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 4000.00
- ሎት 3፡– የፅዳት ዕቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 4000.00
- ሎት 4፡– የህትመት ጨረታ ማስከበሪያ ብር 4000.00
- ሎት 5፡– ጥገና የሚደረግላቸው ኮንፒውተር፣ ፕሪንተር፣ የፎቶኮፒ ማሽኖችና ሌሎች የጥገና እቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 4000.00
- ሎት 6፡– ቋሚ የኤሌክትሪክ ዕቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5000.00
- ሎት 7፡– ቋሚ የፈርኒቸር ዕቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5000.00
- ሎት 8፡– የተሽከርካሪ የኪራይ አገልግሎትና የመኪና እና የጄኔሬተር እቃ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5000.00
- ሎት 9፡– የመድሀኒትና ላብራቶሪ ሪኤጀንቶች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5000.00
- ሎት 10፡ የተለያዩ ቋሚ አላቂ የካፌ እቃዎች (የሻይ ብርጭቆ፣ የቡና ስኒ፣ ረከቦት፣ ትሪ እና የተለያዩ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5000.00
- ሎት 11፦ የተለያዩ የደንብ ልብስ ስፌት የጨረታ ማስከበሪያ ብር 4000.00
- ሎት 12፡– የሙሉ ህንጻ የውጭ ግድግዳ የቀለም ቅብና የተለያዩ እድሳቶች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 5000.00 ብቃት ያላቸው በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ አገልግሎት መፈፀም ይፈልጋል።
በዚህም መሰረት፣
1. 1. በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ በመንግስት ግን አስ ኤጀንሲ ድህረ ገፅ ላይ በአቅራቢዎች ምዝገባ ዝርዝር የተመዘገበ የቲንና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
2. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታው ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
3. ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት አንስቶ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል በልደታ ክፍለ ከተማ የወ/ሮ በለጥሻቸው የህዝብ ጤና ጣቢያ አዲሱ ህንፃ አንደኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 101 (ፋይናንስ) ቢሮ በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
4. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን ኦሪጅናልና ኮፒ በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያ ከወጣበት እለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
5. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአስራ አንደኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ 4፡30 ሰዓት በወ/ሮ በለጥሻቸው የህዝብ ጤና ጣቢያ አዲሱ ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201 ይከፈታል፤ የመክፈቻ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የበዐል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ ይከፈታል።
6. ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን እቃዎች ለእያንዳንዱ ከቫት ውጪና ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።
7. የዘገየ ጨረታና በመክፈቻው ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም፡፡
8. ተጫራቾች ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ባሉት ቀናቶች የተወዳደሩበትን ዕቃ ናሙና ማስገባት አለባቸው ናሙና ያልቀረበበት ጨረታ ዋጋ አይኖረውም።
9. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈፃሚው መስሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
10.መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ለማብራሪያ ጥያቄ የመ/ቤቱ ስልክ 011-8-54-9237
በልደታ ክፍለ ከተማ የወ/ሮ በለጥሻቸው የህዝብ ጤና ጣቢያ