በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በ2018 በጀት ዓመት የተለያዩ ዕቃዎችን መግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen(Sep 07, 2025)

Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።

1ኛ ዙር ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ 

ለኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ 2018 በጀት ዓመት 1 ዙር ግልጽ ጨረታ ማውጣት ስለፈለገ የሚከተሉት የቢሮና የስልጠና ግባቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

ስለዚህ

  • ሎት 1- ቋሚ የቢሮ ዕቃ-10,000
  • ሎት 2- አላቂ የቢሮ ዕቃ –10,000
  • ሎት 3 የክሊኒክ እና የእስፖርት ዕቃዎች 10,000
  • ሎት 4-የፅዳት እቃዎች-5,000
  • ሎት 5 የሆቴል ዲፓርትመንት ዕቃዎች-20,000
  • ሎት 6 የአይሲቲ እቃዎች–20,000
  • ሎት 7 የኮንስትራክሽን እቃዎች-20,000
  • ሎት 8 የጋርመንት እቃዎች -20000
  • ሎት 9 የአግሮ እቃዎች – 20,000 በመሆኑ
  • ሎት 10 የማኑፋክቸሪንግ እና ፈርኒቸር እቃዎች -20,000
  • ሎት 11 የቢሮ ዕቃዎች ጥገና እቃዎች— 5,000
  • ሎት 12 የመኪና ጥገና10,000
  • ሎት 13 ህትመት 10,000 በመሆኑ
  • ሎት 14 የውሀ ቁፋሮ –40,000
  • ሎት 16 የመኪና ኪራይ10,000
  1. ተጫራቾች በአቅራቢነት በመንግስት ኤጀንሲ የተመዘገቡ መሆኑን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
  2. በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለውና የዘመኑ የንግድ ግብር ከፋይ ፈቃድን ያደሰና ማስረጃው ግልጽ የሆነና የሚነበብ ኮፒ ማቅረብ የሚችል
  3. ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ስለመሆኑ የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል መሆን አለባቸው
  4. የጨረታ ሰነድ በድርጅቱ ስም ያልገዛ ተወዳዳሪ በጨረታ መሳተፍ አይችልም
  5. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የጨረታ ሰነድን በየሎቱ የማይመለስ 400 /አራት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ
  6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተረጋገጠ ብቻ በየሎቱ አሰርተው ማቅረብ ይኖርባቸዋል
  7. ጨረታውን ከወጣበት ቀን አንስቶ 10 /አስር/ተከታታይ የስራ ቀናት የሚቆይ ሲሆን 11ኛው ቀን 4:00 ሰአት ላይ ታሽጎ 4:30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል 11ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆና በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል
  8. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ዋጋቸው ኮሌጅ ባዘጋጀው ሰነድ ላይ ቫትን ያካተተ /ዋጋ የሚለውን በግልጽ ሞልቶ ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ይህን በግልጽ ሞልተው ያላቀረቡ ተጫራቾች ዋጋው ቫትን ያካተተ ነው ተብሎ ይወሰዳል
  9. ተጫራቾች በሰነዱ ላይ እንደተጠቀሰው ቴክኒካል ዶክመንት ወይም ሳምፕል ማቅረብ ይኖርባቸዋል
  10. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ፋይናንሻልና ቴክኒካል ዋናውንና ኮፒውን በተናጠል በታሽገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል ተጫራቾች በራሳቸው ትራንስፖርትና አውራጅ የጉልበት ሰራተኛ በመመደብ ለኮሌጅ ንብረት ግምጃ ቤት ያስረክባል
  11. ኮሌጅ የተሻለ አማራ ካአገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
  • ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 0113697215
  • አድራሻ አዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ከዘነበወርቅ ወደ ወይራ ሰፈር በሚወስደው መንገድ 250ሜትር ወደ ግራ ገባ ብሎ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ኮልፌ ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ