Your cart is currently empty!
የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ የተለያዩ የእህል (የበቆሎ እና የዳጉሳ) አጨዳና ምርት ማጓጓዝ አገልግሎት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Sep 16, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡– 0SE/NCB/002/2018
የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ የተለያዩ የእህል (የበቆሎ እና የዳጉሳ) አጨዳና ምርት ማጓጓዝ አገልግሎት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም አስፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ተጫራቾች፡–
- የንግድ ምዝገባ ሰርተፊኬት፤
- የዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፤
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት፤
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (Tin No)፤
- የአቅራቢነት ማስረጃ (Supplier List)፤
- የሚፈለግባቸውን የመንግሥት ግብር ስለመወጣታቸው የሚገልጽ ማስረጃ፣ ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ አለባቸው።
ተጫራቾች የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ሰነዱን በመግዛት በ16ኛው የሥራ ቀን ይከፈታል። ሰነዱን መግዛት የምትችሉት ከኢንተርፕራይዙ ዋና መ/ቤት ጎተራ አጎና ሠራዊት ሲኒማ አጠገብ ባለኬር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 402 ሲሆን ጨረታ ሰነድ መሸጫ ዋጋ የማይመለስ 200 ብር ሲሆን ሰነዱ የሚሰጠው በሶፍት ኮፒ ነው። ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያቸውን በታሸገ ፖስታ በማድረግ በተጠቀሰው ቀን ከ2፡30 እስከ 8፡00 ሰዓት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በማስገባት በጨረታው እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል።
የጨረታው ሳጥን በዕለቱ በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢንተርፕራይዙ ዋና መ/ቤት ጎተራ እጎና ሠራዊት ሲኒማ አጠገብ ባለኬር ህንፃ /Baleker Tower/ 6ኛ ፎቅ በሚገኘው የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ቁጥር 603 ይከፈታል።
ኢንተርፕራይዙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ ማብራሪያ ስልክ ቁጥር፡– 011-466-2527/ 011-416-0309 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
የኦሮሚያ ምርጥ ዘር ኢንተርፕራይዝ