በኮ/ቀ/ክ/ከተማ የወረዳ 02 የህዳሴ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የተለያዩ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen(Sep 20, 2025)

 Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።

የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር 001/2018

በኮ/ቀ/ክ/ከተማ የወረዳ 02 የህዳሴ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ2018 ዓ ም በጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

  • ሎት 1 የደንብ ልብስ ፣
  • ሎት 2.አላቂ የቢሮ እቃዎች፣
  • ሎት 3የህትመት ሥራ፣
  • ሎት 5.አላቂ የትምህርት እቃዎች፣
  • ሎት.6.የጽዳት እቃዎች፣
  • ሎት 7.የት/ት መሣሪያዎች መግዣ፣
  • ሎት 8 ፕላንት ማሽነሪ፣ 
  • ሎት 9.የተገጣጣሚ እና ቁሳቁስ መግዣ፣
  • ሎት.10 ኤሌክትሮኒከስ ጥገና፣
  • ሎት 11 የተገጣጣሚ እና ቁሳቁስ ጥገና፣
  •  ሎት.12.መሰረተልማት፣
  •  ሎት 13.የጉልበት እና የትራንስፖርት፣
  • ሎት.15.ልዩ ልዩ ክፍያዎች

በዚህ መሰረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈረት የምታሟሉ ተጫራቾች መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

  1. ተጫራቾች ከሥራው ዘርፍ ጋር አግባብነት ያለው የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያለው የዘመኑ ግብር መክፈላቸውን የሚገልጽ ወቅታዊ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል፤
  2. ት/ቤቱ በሚሸጠው ሰነድ ላይ ያለውን ማንኛውንም መመሪያ በማጤን እና የሚመለከተውን በመሙላት፣ ማህተም በማድረግ፣ ሰነዱን በሙሉ በታሸገ ፖስታ ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን በተለያየ ፖስታ በማድረግ በኮ/ቀ/ክ/ከተማ የወረዳ 02 የህዳሴ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ቢሮ ቁጥር 7 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅበታል፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለመግዛት በየሎቱ የማይመለስ 100 ብር /አንድ መቶ ብር/ ከፍለው መውሰድ ይችላሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታዎች ለመሳተፍ የጨረታ ማስከበሪያ /cpo) የብር መጠን በየሎት ለእያንዳንዱ ሎት1. 18,000፣ ሎት2. 21,000፣ ሎት 3 .2,000፣ ሎት.5 .14,000፣ ሎት.6. 18,000፣ ሎት.7. 13,000፣ ሎት 8. 17,000፣ ሎት.9. 18.000፣ ሎት 10. 2.000፣ ሎት11. 9.000 ፣ ሎት12 .12,000 ፣ ሎት 13 .6,000፣ ሎት15. 3,000 ማስያዝ አለባቸው፡፡
  5. በጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በጨረታ ማስከበሪያ በውል ማስከበሪያ እና በቅድሚያ ከፍያ ዋስትና ምትክ ካደራጀው ተቋም በኃላፊ ብቻ የተፈረመ የዋስትና ደብዳቤ ተቀባይነት ሲኖረው በሥራ ሂደት የሚፈረም ደብዳቤ ተቀባይነት የለውም፡፡
  6. ማንኛውም ተጫራች የሚጫረቱበት እቃ ላይ የሚያቀርቡት የእቃ ናሙና በግልጽ የሚታይ ፎቶ፣ ቦታው ላይ እና የሚሸጠው ሰነድ ላይ በወጣው መሰረት ማሳየትና ማቅረብ አለበት፡፡
  7. ተጫራቾች በሚያቀርቡት ማንኛውም ናሙና ላይ ምንም አይነት የድርጅቱ ስም፣ ኮድም ሆነ ማህተም የሚገልጽ ነገር ቢያስቀምጡበት ከውድድር ውጪ እንደሚሆኑ እንገልጻለን፡፡
  8. የኤሌክትሮኒክስ ጥገና ፣ የቁሳቁስ ጥገና፣ የትራንስፖርት እና ጉልበት ላይ አሸናፊ የሚሆኑት ውላችን የአንድ ዓመት መሆኑ ይታወቅ፡፡
  9. ጨረታው ከወጣበት 23/01/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ የሥራ ቀናት በአየር ላይ ቆይቶ በ11ኛው ቀን በ3፡30 ሰዓት ታሽጎ በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት በፋይናንስ ክፍል ይከፈታል፡፡
  10. ተጫራቾች ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜ እና እሁድ የበዓላት ቀን የሚውል ከሆነ ቀኑን አሳልፈን የምንከፍት መሆኑን ማወቅ አለባቸው::
  11. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል /በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

አድራሻ፡- ካራ ቆሬ ወደመደኃኒዓለም ቤተከርስቲያን መሄጃ ፖሊስ ጣቢያውን አለፍ ብሎ

ተጨማሪ መረጃ፦ 011 369 5428/ 011 369 5841/

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የወረዳ 02 የህዳሴ, 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፋይናንስ ግዥ ቢሮ።

በኮ/ቀ/ክ/ ከተማ የወረዳ 02 የህዳሴ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት