Your cart is currently empty!
የአባይ ኮንስትራክሽን ኃላ/የተ/የግ/ማህበር በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት በአማራ ክልል በሚገኙ የተለያዩ የመስኖና መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ አገልግሎት የሚውሉ ማሽነሪ፣ ቀላል እና ከባድ ተሸከርካሪዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በኪራይ ማሰራት ይፈልጋል
Addis Zemen(Sep 20, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የተሽከርካሪ እና ማሽነሪ ኪራይ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር አኮኃ/ብግጨ/01/2018
የአባይ ኮንስትራክሽን ኃላ/የተ/የግ/ማህበር በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት በአማራ ክልል በሚገኙ የተለያዩ የመስኖና መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ አገልግሎት የሚውሉ ማሽነሪ፣ ቀላል እና ከባድ ተሸከርካሪዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በኪራይ ማሰራት ይፈልጋል።
ስለዚህ ድርጅቱ የሚከተሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን ይጋብዛል።
የህጋዊነት ማስረጃዎችን ማለትም በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ስራ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው፣ ለማሽነሪዎችና ከባድ ተሽከርካሪዎች ለመወዳደር የተጨማሪ እሴት ታከስ የምዝገባ ሰርትፍኬት ማቅረብ አለባቸው። ነገር ግን ለቀላል ተሽከርካሪዎች የቫት ተመዝጋቢ ካልሆኑ በስማቸው የታተመ ደረሰኝ ወይም TOT ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፤ የሚያከራዩት ማሽነሪ ተሽከርካሪዎች የባለቤትነት ማረጋገጫ (ሊብሬ) ኮፒውን በማያያዝ እና ለማመሳከሪያነት ኦሪጅናል ሊብሬ በውል ወቅት ማሳየት አለባቸው
2. የጨረታውን ዝርዝር ሁኔታ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል። የሚያስፈልጉ የተሽከርካሪዎችና የማሽነሪዎች ብዛት በየቀጠናው (ከባቢያዊ ምድብ) እንደ ፕሮጀክቶች ቁጥር እየታየ የሚወሰን ሆኖ አይነታቸው እንደሚከተለው ይሆናል።
ተ.ቁ |
የተሽከርካሪ /ማሽነሪ/ አይነት |
የስሪት ዘመን (እ.ኤ.አ) |
የክፍያ ሁኔታ |
የሚሰሩበት ቦታ/ፕሮጄክት |
1 |
ኮብራ መኪና |
2000 እና በላይ |
በቀን |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
2 |
ዳብል ካፕ |
1999 እና በላይ |
በቀን |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
3 |
ሲንግል ጋቢና (1HZ) |
1999 እና በላይ |
በቀን |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
4 |
ስቴሽን ዋገን- ላንድ ክሮዘር |
1998 እና በላይ |
በቀን |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
5 |
ሚኒ ካፕ (ኤክስትራ ካፕ) |
2000 እና በላይ |
በቀን |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
6 |
ገልባጭ መኪና 16 ሜ/ኩ/129 ኩንታል እና በላይ |
ከ2008 እና በላይ |
በቀን/በሜ3 |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
7 |
አይሱዚ ቅጥቅጥ ለሰው ጭነት |
ከ2000 እና በላይ |
በቀን |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
8 |
አይሱዚ ደረቅ ጭነት |
ከ2000 እና በላይ |
በቀን |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
9 |
ኤከስካቫተ ርበአካፋ/በጃከሃመር |
ከ2008 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
10 |
ትራከ ሚክሰር/ኮንክሪትሚከሰር |
ከ2005 እና በላይ |
በወር |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
11 |
ዶዘር |
2011 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
12 |
ሎደር |
ከ2012 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
13 |
ሃፍ ክሬን |
ከ2008 እና በላይ |
በወር |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
14 |
ግሬደር ከካት ዉጭ |
ከ2012 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
15 |
ካት ግሬደር |
2008 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
16 |
ስሙዝ ኮምፓክተር |
ከ2008 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
17 |
ሽፕ ፉት ኮምፓክተር |
ከ2008 እና በላይ |
በሰዓት |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
18 |
ሻወር ትራክ |
ከ2000 እና በላይ |
በወር |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
19 |
ፊውል ትራክ |
ከ1998 እና በላይ |
በወር |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
20 |
ትራክተር |
ከ2008 እና በላይ |
በወር |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
21 |
ሚኒ ባስ |
ከ2006 እና በላይ |
በወር |
ለቀጠና 02 እና ለቀጠና 08 |
22 |
ሎቤድ ትራከ |
ከ2008 እና በላይ |
በትሪፕ |
በአማራ ክልል ውስጥ በሚገኙ ፕሮጀክቶች |
1. ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች በኪራይ የሚገቡት ለመስኖ ፣መጠጥ ውሃ ግንባታ ፕሮጀክቶች 8ለሰርቪስ እና ለሱፐርቪዥን አገልግሎት ነው።
2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ባህር ዳር ቀበሌ 16 ህዳሴ ሰፈር አመልድ ጋራጅ አባይ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር ቢሮ ከግዥ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 19 ማግኘት ይቻላል። እንዲሁም በኩባንያዉ ዌቭሳይት ማግኘት ይችላሉ።
3. ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው የተለያዩ ተሽከርካሪዎች ማሽነሪዎች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid Bond) በባንክ በተረጋገጠ ትዕዛዝ (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (unconditional Bank Guarantee) በጨረታ ሰነዱ የተቀመጠውን የገንዘብ መጠን በአባይ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር ስም ማስያዝ አለባቸው።
4. ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ በተገለፀው መሰረት የጨረታውን ሰነድ በታሸገ ፖስታ ለማሽነሪና ተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት ጨረታ ተብሎ ትክክለኛ ስምና አድራሻ በመፃፍ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት እስከ 15ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት በስራ ሰዓት ባህር ዳር ቀበሌ 16 ህዳሴ ሰፈር አመልድ ጋራጅ በሚገኘው የአባይ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር ዋና መ/ቤት ግዥ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 19 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ።
5. ጨረታው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ተከታታይ ቀን ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ይዘጋል፤ በ15ኛው ተከታታይ ቀን ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 19 ይከፈታል።
6, 15ኛው ቀን የበዓል ቀን ወይም እሁድና ቅዳሜ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ 8፡30 ይከፈታል።
7. ተጫራቾች በጨረታው ደንብና መመሪያ መሠረት ጨረታቸውን ማቅረብ አለባቸው። ከጨረታው ደንብና መመሪያ ውጭ የሚቀርብ ማንኛውም ጨረታ ተቀባይነት የለውም።
8. ተጫራቾች የሚያከራዩትን የማሽንና ተሽከርካሪ አይነት ብዛቱን ጭምር በዋጋ መሙያ ፎርሙ ላይ በግልጽ ማስቀመጥ አለባቸው።
9. አሸናፊው ድርጅት በጨረታ በተወዳደረበት ተሽከርካሪ እና ማሽነሪ ቁጥር ልክ መሣሪያዎችን ማቅረብ ይችላል።
10. አንድ ተወዳዳሪ ከራሱ መሣሪያና ተሽከርካሪ ውጭ የሚያቀርብ ከሆነ ከፍትህ ጽ/ቤት ሕጋዊ ውክልና እና የባለቤትነት ማስረጃ ሊብሬ ማያያዝ አለበት።
11. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊልም የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
12. በጨረታው ለመሳተፍ ለሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከግዥ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 19 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም https://www.abayconstruction.org.et/auction-bid/ በስልክ ቁጥር 09 91 02 14 30 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።
አባይ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር