የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፎርክሊፍት፣ የሠራተኛ ሰርቪስ፣ እና የከተማ ውስጥ ጭነት ተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል


Addis Zemen(Sep 26, 2025)

Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።

የፎርክሊፍት፣ የሠራተኛ ሰርቪስ፣ እና የከተማ ውስጥ ጭነት

ተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር NEBE/NCB/03/2018

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የመስክ ሥራዎችን ለማከናወን ፎርክሊፍት፣ የሠራተኛ ሰርቪስ እና የከተማ ውስጥ ጭነት አገልግሎት የኪራይ አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡

በዚህም መሰረት፡

  • ሎት አንድ፡የፎርከሊፍት
  • ሎት ሁለት፡የሠራተኛ ሰርቪስ እና ፒካፕ
  • ሎት ሦስት፣የከተማ ውስጥ ጭነት ተሽከርካሪ ኪራይ አገልግሎት ግዥ ለመፈፀም
  1. በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ጨረታው እስከሚዘጋበት ቀን ድረስ ባሉት የስራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300.00 /ሦስት መቶ ብር/ በመክፈል ከቦርዱ ግዥ ስራ ክፍል ቢሮ ቁጥር 107 ማግኘት ይችላሉ።
  2. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ ተጨማሪ እሴት ታክስና የግብር ከፋይ ምዝገባ ሠርተፍኬት፣የዘመኑ ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ሠርተፍኬት እና በመንግስት ኤሌክትሮኒክስ ግዥ በአቅራቢነት የተመዘገቡ ስለመሆኑ የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
  3. ተወዳዳሪዎች በሚወዳደሩበት መስክ ያላቸውን መልካም አፈጻጸም የሚያሳይ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  4. የጨረታ ሰነዱን ከቦርዱ የግዥ አስተዳደር የሥራ ክፍል በመውሰድ ሞልተው አግባብ ካለው አካል በመፈረም ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት አንድ ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር) ለሎት ሁለት ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) ለሎት ሦስት ብር 30,000.00 (ሰላሳ ሺህ ብር) በባንክ የተረጋገጠ ዋስትና ወይም ሲፒኦ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
  6. ተወዳዳሪዎች ቴክኒካል ፕሮፖዛል እና ፋይናንሻል ፕሮፖዛል በተለያየ ፖስታ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣
  7. ጨረታው ጥቅምት 04 ቀን 2018 . ከቀኑ 800 ተዘግቶ በዕለቱ ከቀኑ 830 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፤
  8. ቦርዱ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፣

አድራሻችን፡ቦስ ፍላሚንጎ ካፌ ገባ

ስልክ ቁጥር፡-+251 11 515 3468

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ