የመልሳ ኖኖ ክፍለ ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት አላቂ ዕቃ፣ የደንብ ልብስ፣ ፈርኒቸር፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ስቴሽነሪዎች፣ እና የፅዳት ዕቃዎች ለፍ/ቤቱ የሚያገለግል አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen(Oct 12, 2025)

ከስር የተቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ። Please read the detailed instructions below. 

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

የመልሳ ኖኖ ከፍለ ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ፍ/ቤቱ የሚጠቀመው 

  • አላቂ ዕቃ፣
  • የደንብ ልብስ፣
  • ፈርኒቸር፣
  • ኤሌክትሮኒክስ፣ 
  • ስቴሽነሪዎች፣ እና የፅዳት ዕቃዎች ለፍ/ቤቱ የሚያገለግል አወዳድሮ መግዘት ይፈልጋል።

ስለዚህ በጨረታው መወዳደር የምትፈልጉ ነጋዴዎች እና ባለሀብቶች ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡

  1. ተጫራቾች በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው እና የታደሰ እንዲሁም የሚፈለግባቸውን ግብር አጠናቀው ስለመከፈላቸው በቂ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. ተጫራቾች ዝርዝር የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት የመልካ ኖኖ ከፍለ ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት ዘወትር በሥራ ሰዓት የማይመለስ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስረከቢያ ብር 50,000(ሃምሳ ሺህ ብር) በባንክ በተመሰከረለት CPO የመልካ ኖኖ ክፍለ ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት ስም አዘጋጅቶ ከማጫረቻ ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  4. የጥቃቅን እና አነስተኛ ማኅበራት የተጠቀሰውን የጨረታ ማስከበሪያ መጠን በመጥቀስ ካደራጃቸው መ/ቤት በቀጥታ ለመ/ቤታችን የዋስትና ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርበታል፤ የጥቃቅን እና አነስተኛ ማኅበራት ለረታ ማስከበሪያ ከቀበሌ የሚመጣ ደብዳቤ ተቀባይነት የለም፡፡
  5. ተጫራቾች ሰነዱን ከገዙ በኋላ የሚሸጡበትን ዋጋ በመጥቀስ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ በተባለው ቀን ውስጥ ለጨረታ ለተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች የተሟላ ዋጋ ስርዝ ድልዝ መሆን የለበትም፡፡
  7. ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ(VAT) ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፤ እንዲሁም ተጫራቾች የሚሰጡሉት ዋጋ ከትን 15 ያካተተ መሆን አለበት፡፡
  8. ተጫራቾች ያሸነፉትን ዕቃዎች መስሪያ ቤቱ ባዘጋጀው ቦታ ድርስ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል።
  9. ተጫራቾች ያሸነፉትን ዕቃዎች ፍ/ቤቱ ካዘዘ በኋላ የታዘዘው ዕቃ አሸናፊው ለናሙና ለፍ/ቤቱ ማቅረብ የሚችል እና ገቢ የሚሆነው አስፈላጊውን ጥራት ማሟላቱን በባለሙያ ሲረጋገጥ ይሆናል፡፡
  10. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዕቃ ከእሰቶካቸው መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
  11. የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በቀኑ 8፡00 ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
  12. ከላይ የተገለፀው የመክፈቻ ቀን በዓል ወይንም የሰንበት ቀን ላይ ከዋለ ጨረታው የሚከፈተው በቀጣዩ የሥራ ቀን ይሆናል፡፡
  13. ፍ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ወይም ምርጫ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 251 11 260 1258

በሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመካ ኖኖ ክፍለ ከተማ

ወረዳ ፍርድ ቤት