Your cart is currently empty!
በአዲስ አበባ ከተማ የለሚ ኩራ ክፍል ከተማ አስተዳደር ጤ/ጽ/ቤት የተለያዩ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Oct 14, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ቅጽ
የግዢ ጨረታ መለያ ቁጥር 01/2018 ዓ/ም
በአዲስ አበባ ከተማ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር /ጤ/ጽ/ቤት ወረዳ 03 የመሪ ጤና ጣቢያ የ2018 ዓ/ም የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት በግልፅ ጨረታ ግዥ ለመፈፀም ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት እቃዎች
- ሎት – 1 የደንብ ልብስ እና ስፌት፣
- ሎት – 2 አላቂ የጽህፈት መሳሪያዎች፣
- ሎት -3 የጽዳት ዕቃዎች፣
- ሎት – 4 የህትመት ስራዎች፣
- ሎት – 5 አላቂ የህክምና ዕቃዎች፣
- ሎት -6 ልዩ ልዩ ዕቃዎች፣
- ሎት – 7 የጥገና እቃዎች፤
- ሎት– 8 ቋሚ የቢሮ እቃዎች
መ/ቤቱ ባወጣው እስፔስፊኬሽን መሰረት፤
ሎት– 9 ቋሚ የህክምና እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚህ መሰረት በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ሕጋዊ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ መሆን አለባቸው፡፡
በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች
- ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩበትን ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር ለመክፈላቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
- በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚ/ር በአቅራቢነት የተመዘገበ እና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣
- የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያለው፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
- በማንኛውም ግልፅ ጨረታ ላይ ያልታገዱ መሆን አለበት፡፡
- ተጫራቾች ከዚህ በታች የተጠቀሰውን የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ CPO ማቅረብ አለባቸው፡፡
|
ሎት ቁጥር |
የሎት ዝርዝር |
የተጠየቀው የጨረታ ማስከበሪያ |
|
ሎት 1 |
የደንብ ልብስና ስፊት |
ብር 10,000.00 |
|
ሎት 2 |
አላቂ የጽህፈት መሳሪያዎች |
ብር 10,000.00 |
|
ሎት 3 |
የጽዳት ዕቃዎች |
ብር 10,000.00 |
|
ሎት 4 |
የህትመት ስራዎች |
ብር 10,000.00 |
|
ሎት 5 |
አላቂ የህክምና ዕቃዎች |
ብር 10,000.00 |
|
ሎት 6 |
ልዩ ልዩ ዕቃዎች |
ብር 6,000.00 |
|
ሎት 7 |
የጥገና ዕቃዎች |
ብር 10,000.00 |
|
ሎት 8 |
በቋሚ የቢሮ እቃዎች |
ብር 20,000.00 |
|
ሎት 9 |
ቋሚ የህክምና እቃዎች |
ብር 20,000.00 |
7. የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በየሎቱ የማይመለስ ብር 200.00/ ሁለት መቶ ብር / በመክፈል የተዘጋጀውን ሰነድ ከተቋሙ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 51 እየቀረቡ መግዛት ይችላሉ፡፡
8. ተጫራቾች ጨረታ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 10/አስር/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በመሪ ጤና ጣቢያ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 55 ድረስ በመምጣት ዋጋው የተሞላበትን የጨረታ ሰነዱን ዋናውንና ፎቶ ኮፒ ለየብቻው በማሸግ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
9. ጨረታው በ10ኛው ቀን ከጥዋቱ 2፡30 እስከ 7፡50 ድረስ ክፍት ሆኖ በዚሁ ቀን ከሰዓት በኋላ 8፡00 ላይ ታሽጎ በዚሁ እለት 8፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን እና በተጠቀሰው ተመሳሳይ ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
10. ተጫራቾች ላሸነፉባቸው ጠቅላላ ዋጋ የውል ማስከበሪያ 10% ማስያዝ አለባቸው።
11. ተጫራቾች ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ለሚወዳደሩበት ናሙና ለሚቀርብባቸው ዕቃዎች ናሙና ማቅረብ አለባቸው፡፡ ናሙና የማይቀርብባቸው ቋሚ ዕቃዎች መስሪያ ቤቱ ባቀረበው ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ አለባቸው በተጨማሪም በፎቶ /በማንዋል አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
12. በጨረታ አሸናፊ ሆኖ የተመረጠ ድርጅት ያሸነፈበትን ዕቃ በራሱ ትራንስፖርት ወረዳ 03 መሪ ጤና ጣቢያ ድረስ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
13. መ/ቤቱ ለጨረታ ከቀረበው ዕቃ እስከ 20% የመቀነስም ሆነ የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
14. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡- እያንዳንዱ ዋጋ ሲሞላ ቫትን ጨምሮ መሆን አለበት ዘግይቶ የመጣ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም
አድራሻ፡- ለሚ ኩራ/ክ/ከ/ወረዳ 03 መሪ ጤና ጣቢያ አያት አደባባይ አለፍ ብሎ ወደ አራብሳ
በሚወስደው አስፓልት ዞን 5ት መንገድ 12 በኮሮኮንች መግቢያ መንገድ 1500 ሜትር ገባ ብሎ ይገኛል።
ስልክ ቁጥር፡- 09 10 51 38 85
በአዲስ አበባ ከተማ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር /ጤ/ጽ/ቤት