Your cart is currently empty!
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፋ/ኢ/ል/መምሪያ ለ24 (ሃያ አራት) በ2018 በጀት ዓመት ባቀዱት ዕቅድ መሠረት በከተማ ውስጥ በርካታ አለም አቀፍና ሀገር አቀፍ እንግዶች እና የፌዴራልና የክልሎች አመራሮች እንዲሁም የከተማ ምክር ቤት ጉባኤዎች ወዘተ…ስብሰባዎችን ለማስተናገድ እና የተለያዩ ሥራዎችን በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት እና መግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Oct 14, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የጨረታ ማስታወቂያ
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፋ/ኢ/ል/መምሪያ ለ24 (ሃያ አራት) በ2018 በጀት ዓመት ባቀዱት ዕቅድ መሠረት በከተማ ውስጥ በርካታ አለም አቀፍና ሀገር አቀፍ እንግዶች እና የፌዴራልና የክልሎች አመራሮች እንዲሁም የከተማ ምክር ቤት ጉባኤዎች ወዘተ…ስብሰባዎችን ለማስተናገድ እና የተለያዩ ሥራዎችን በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት እና መግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚህ መሠረት፡–
1. የመድረክ ዲኮሬሽን ሥራ ለማሰራት፡– ሎት/ምድብ 1(አንድ)
2. የመስተንግዶ ግዥ፡–ሎት/ምድብ 2(ሁለት)
3. የመጋረጃ እና ምንጣፍ ሎት/ምድብ 3(ሶስት)
4. የመኪና ዲኮር እና አልባሳት ሎት/ ምድብ 4(አራት)
5. ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ግዥ ሎት/ምድብ 5(አምስት)
ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡–
1. በሥራ መስኩ ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፍቃድ፤ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉና የዘመኑን ግብር መክፈላቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
2. ተጨማሪ እሴትታክስ (VAT) ተመዝጋቢየሆኑ፣
3. የአቅራቢነት ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው፣
4. የታክስ ክሊራንስ ማቅረብ አለበት፤
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በየሎቱ/በየምድቡ 30,000 (ሰላሳ ሺህ ብር) በባንክ የተረጋገጠ (የተመሰከረ) ሲፒኦ (CPO) ወይም ቢድ ቦንድ ብቻ ከጨረታ ሰነድ ጋር ታሽጎ ማቅረብ አለበት፡፡
6. የጨረታ ሰነዱ ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፋይ/ኢኮ/ልማት መምሪያ አራተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 54 (ግዥና ንብረት አስተዳደር ዋና ሥራ ሂደት) በመቅረብ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 /ለአስር/ ተከታታይ ቀናት ብር 400 (አራት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
7. ጨረታ ሰነዱ በሰም ለየብቻቸው በታሸገ ኤንቨሎፕ አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ (ፋይናንሻል) በመያዝ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 /አስር / ተከታታይ ቀናት ውስጥ ጨረታውን በግዥ ኬዝ ቲም ቢሮ ቁጥር 54 ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
8. ጨረታው በ11ኛው /በአሥራ አንደኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ታሽጎ በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበትም ሆነ ባልተገኙበት በቢሮ ቁጥር 54 ይከፈታል፡፡ ይህ ቀን ቅዳሜ ወይም እሁድ እንዲሁም የበዓል ቀን ከሆነ ደግሞ በሚቀጥለው ሥራ ቀን ጨረታው ይከፈታል፡፡
9. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ፡– ስልክ ቁጥር፡-046 212 1334 ደውለው ይጠይቁ።
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፋይ/ኢኮ/ልማት መምሪያ
ሀዋሳ