በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የዓለም ብርሃን የመ/ደ/ት/ቤት ለ2018 ዓ.ም አገልግሎት የሚውሉ አላቂ የቢሮ ዕቃዎች፣ የደንብ ልብስ፣ ሌሎች አላቂ ዕቃዎች፣ አላቂ የህክምና ዕቃዎች፣ ቋሚ ዕቃዎች እና የትምህርት ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል


Addis Zemen(Oct 15, 2025)

ከስር የተቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ። Please read the detailed instructions below. 

የግልፅ የዕቃ ግዢ ጨረታ ማስታወቂያ 001/2018

በአቃቂ/ቃ/ክ/ከተማ የዓለም ብርሃን የመ/ደ/ት/ቤት ለ2018 ዓ.ም አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ

  • በሎት 1 አላቂ የቢሮ ዕቃዎች
  • በሎት 2 የደንብ ልብስ
  • በሎት 3 ሌሎች አላቂ ዕቃዎች
  • በሎት 4 አላቂ የህክምና ዕቃዎች
  • በሎት 5 ቋሚ ዕቃዎች
  • በሎት 6. የትምህርት ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

 በዚሁ መሰረት ተጫራቾች

  • በመንግስት እቃ አቅራቢነት ተመዝግቦ የምስክር ወረቀት ያለው
  • ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው
  • የዘመኑን ግብር የከፈሉና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
  • ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸውንና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
  • ተጫራቾች የማይመለስ 100 /አንድ መቶ ብር /በመክፈል ጨረታ ሰነዱን ከት/ቤቱ ፋይናንስ ክፍል መውሰድ ይችላሉ፡፡
  • ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በገዙት ሰነድ ባለው ዋጋ ማቅረቢያ ላይ በግልፅ በመሙላት በመጨረሻ ቦታ ላይ ስምና ፊርማ በማኖር በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ከ2፡30 እስከ 10፡30 ከት/ቤቱ ፋይናንስ ክፍል ማስገባት ይችላሉ፡፡
  • ተጫራቾች በገዙት ሰነድ ባለው ዋጋ ማቅረቢያ ላይ በግልፅ በመሙላት ዋናውንና ኮፒ በማድረግ ማስገባት ይኖርባቸዋል ኮፒ ያላደረገ ተጫራች ለውድድር አይቀርብም
  • ተጫራቾች የሚያሲዙት የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ በሚያስገቡት ጨረታ ጠቅላላ ዋጋ 1% በማሰራት

በሎት 1. 1919

በሎት2.  15619

በሎት 3.  16419

በሎት4.  900

በሎት5.  10000

በሎት6.  9040

  • አሸናፊ የሚሆኑ ተጫራቾች የውል ማስከበሪያ /የመልካም አፈፃፀም ዋስትና የጠቅላላ ዋጋ 10% ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  • አሸናፊ ከታወቀ በኋላ ለተሸናፊው ያስያዙትን የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘብ ወዲያውኑ ይመለሳል።
  • ጨረታው የሚከፈተው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በወጣበት በ10ኛው ቀን በ10፡30 ተዘግቶ በ11ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት ይከፈታል።
  • በመስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  • ተወዳዳሪዎች ለውድድር ሲቀርቡ የዕቃዎች ናሙና የግድ ማቅረብ ይገባቸዋል፡፡ ናሙና ለመቅረብ የማይችሉ ዕቃዎች የግድ በፎቶ መቅረብ አለባቸው።
  • ተወዳዳሪዎች ለውድድር ሲቀርቡ የሚያቀርቡት ዋጋ በእያንዳንዱ ዕቃ ዋጋ ቫት ያካተተ መሆን አለበት።
  • ቫት ያላካተተ ተጫራች ለውድድር አይቀርብም።
    ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-4716158/011434-3375 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡ አድራሻ አቃ/ቃ/ደብረዘይት መንገድ ከየሺ ቶታል አስፋልት ገባ ብሎ ልዩ ስሙ አቃቂ አለም ባንክ

በአቃቂ/ ቃ/ክ/ከተማ የዓለም ብርሃን የመ/መካከለኛ ደ/ት/ቤት