Your cart is currently empty!
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በከምባታ ዞን የሀደሮ ከተማ አስ/ር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለሴ/መ/ቤቶች አገ/ት የሚሰጡ ዕቃዎች የጽ/መሳሪያ፣ የኤሌክትሮኒክስ እና ፈርኒቸር ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Addis Zemen(Oct 28, 2025)
Please read the detailed instructions below. ከስር የተጠቀመጠውን እያንዳንዱን መረጃ በጥንቃቄ ያንብቡ።
የጨረታ ማስታወቂያ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በከምባታ ዞን የሀደሮ ከተማ አስ/ር ፋይናንስ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለሴ/መ/ቤቶች አገ/ት የሚሰጡ ዕቃዎች
- ሎት 01 የጽ/መሳሪያ
- ሎት 02 የኤሌክትሮኒክስ
- ሎት 03 ፈርኒቸር ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉበት፣በአቅራቢዎች ውስጥ ተመዝጋቢ የሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ሠርተፍኬትና የግብርከፋዮች መለያ ሠርትፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
2. ተጫራቾች ይህ የጨረታ ጥሪ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሎት ተከታታይ 15 ቀናት በስራ ሰዓት በመገኘት ከመ/ቤታችን በግዥ ኬዝ ቲም ቢሮ ቁ.01 የጨረታ ሰነዱን በ500/አምስት መቶ/ ብር ከፍለው መውሰድ ይችላሉ።
3. በጨረታው የዋጋ ማቅረቢያ ሰንጠረዥ የዋጋ ቅናሽ (Discount) እስካልተጠቀሰ ድረስ የዋጋ ቅናሽ ብሎ መሙላት ቅናሹ ተቀባይነት እንዳይኖረው ያደርጋል።
4. ተጫረቾች የሚወዳደሩበትን ሰነድ አንድ ኦሪጅናልና ሁለት ኮፒ ሲሆን ኮፒውን ማስያዝ ያለበት ሁሉንም የህጋዊነት ፈቃድ ዶክሜንቶችን፣ሲ.ፒ.ኦ እና የሥራ ዝርዝርና ዋጋን አካቶ መያዙን በማረጋገጥ በድምሩ ሦስት ፖስታ ለየብቻ በማሸግ በመ/ቤታችን በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባችኋል።
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 20,000 (ሃያ ሺህ ብር) በባንክ በተረገጋጠ ሲ.ፒ.ኦ፤ በጥሬ ብር፤በኢንሹራንስ እና በቦንድ በማስያዝ ከመጫረቻ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
6. ይህ ጨረታ የሚከፈተው በቀን 09/03/2018 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ታሽጐ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ 4፡30 በጽ/ቤታችን ግ/ን/አስተዳደር ዋና የሥራ ሂደት ቢሮ ይከፈታል።
7. ተጫራቾች በመክፈቻ ሥነ–ሥርዓት ላይ ያለመገኘት የጨረታውን ሂደት አያስተጓጉልም።
8. ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን አቅርቦቶች በአጭር ጊዜ አጠናቀው ማስረከብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል።
9. አንድ ተጫራች ሌላው ያቀረበው ዋጋ መነሻ በማድረግ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም።
10. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በከምባታ ዞን የሀደሮ ከተማ አስ/ር ፋይናንስ ጽ/ቤት